Posts

ለመሆኑ ደኢህዴን የምር ኪራይ ሰብሳቢነትን መዋጋትና የማድረቅ ፍላጎት አለው ወይስ በሙስና ስም የሲዳማ ብሔር ተወላጆችን ለይቶ መምታት ነው ኣላማው ? ለመሆኑ የኪራይ ሰብሳቢዎችስ ማዕከል የት ነው? እስከ አሁን በኪራይ ሰብሳቢዎች ላይ የተወሰዱ ተጨባጭ እርምጃዎች ምንድናቸው?

Image
ሳይገባን ቀርቶ አይደለም የህዝብን ደም የመጠጠ ባለስልጣን ሆኖ ሀዋሳ ከተማን ከሲዳማ እጅ ፈልቅቆ ለማውጣት ሲዳማን የሚያፈንቅልላቸቸው ከሆነ ከሙስና የፀዳ የስርአቱ አርበኛ ተደርጎ መቆጠሩ አይደንቅም፡፡ በአጠቃላይ ለደኢህዴን ሙስናን መዋጋት ማለት በወረዳ ህዝብን የበዘበዘ የህዝብ ጩሄት ሲበዛ በዞን ላይ መሾም፤ የዞኑን በክልል፤ የክልሉን ወደ ፈዴራል አዛውሮ መሾም መሆኑ ከማንም ኢትዮጵያዊ የተሰወረ አይደለም፡፡ በዚህ አይነት ከደቡብ ዞኖች ወደ ክልልና  ወደ ፈዴራል ተሸጋሽገው  ለስልጣን ሽልማት የበቁት ባለስልጣናትና ለሹመት ሽልማት ያበቃቸውን ስራ ለግንዘቤ እንዲረዳ ከብዙ በጥቂቱ እንደሚከተለው አቅርበናል፡፡ 1 የደኢህዴን መጨረሻ ስልጣን ደረጃ ላይ የተቀመጡ በአሁኑ ጊዜ በፌዴራል የተሾሙ ባለስልጣናት በልዩ ትዕዛዝ ከሊዝ ደንብና መመሪያ ውጪ ለራሳቸው 425 ካ/ሜ በተጨማሪ ማስፋፊያ ሳይጠይቁ 250 ካ/ሜ ጨምረው በህገ ወጥ መንገድ የያዙት መሬት ከሙስና የጸዳ ይባል ይሆን? 2 እኚው ባለስልጣን ለጓደኞቹና ለብሔሩ ተወላጆች በተመሳሳይ ትዕዛዝና መንገድ ለኢንቨስትመንት የተሸነሸነውን መሬት ወደ መኖሪያ ቦታነት አስቀይረው ለእያንዳንዳቸው 500 ካ/ሜ ያሰጡበትና የመሬት አገልግሎት አጠቃቀም እንዲዛባ ማድረጉ ምን ያስጠይቃል ጃል? ያሸልማል እንጂ፡፡ 3 ለደቡብ ፖሊስ ባንድ መሣሪያ ግዥ ምክንያት 5000,000 ብር የተመዘበረና በተጨባጭ ተደርሶበት ክስ ተጀምሮ ሳለ በልዩ ትዕዛዝ የታፈነ፤ ይባስ ብሎ ይህን ምዝበራ የፈፀመውን ኮሚሽነር መልሶ በመሾም ይህን አድራጎት የታገሉ የፖሊስ አባላት ብላቴ ተወስደው በእኚ ባለስልጣን በበቀል እንዲባረሩ መደረጉ ሽልማት ቢያሰጥ ለምን ይገርማል፡፡ 24 ይህ ኮሚሽነር በዳቶ ኦዳሄ ቀበሌ አርሶ አደሮችን በማፈናቀል 1000 ካ/ሜ
Image
Sidama Hut Construction by tsegayedonna bekele Bamboo tree ( the strong hollow stems of a tropical plant. Use: building, furniture, canes, fishing rods. or a plant with long woody, often hollow, stems that grows in dense clumps and produces bamboo. Native to: tropical and semitropical areas.) It's roof, wall, door, window, celling and so on are all from Bamboo tree. The beauty  of the house from outside and inside reflect the skill and talent of the local Sidama engineers.    The traditional house have two internal arrangements or partitions. The partitions are known as Aldio and Holgie. Aldio is again arranged into two partitions knows as Bosalo and Hadiro. Bosalo services as reception room where there are place to sit, to make fire and sometimes place to sleep.( for gust and Children) The other section which mean Holgie also made to be Ma'na ( bed room) and working place and store. Sidama traditional house foundation and inauguration are accompanied with the festiv

በሲዳማ ዞን ሸበዲኖ ወረዳ የሚገኙ ግንባር ቀደም አርሶ አደሮችና የግብርና ባለሙያዎች ተሸለሙ

በሲዳማ ዞን ሸበዲኖ ወረዳ የሚገኙ  ግንባር ቀደም አርሶ አደሮችና የግብርና ባለሙያዎች ተሸለሙ::አርሶ አደሮቹ ለሽልማት የበቁት በተጠናቀቀው የበጅ ዓመት በቡና ተክል፤ ሰብል ምርት እንዲሁም በእንስሳት እርባታና በባህላዊና ዘመናዊ መስኖ አጠቃቀም ረገድ የላቀ ውጤት በማስመዝገባቸውና መነሻ ካፒታላቸውም ከ5 መቶ ሺህ እሰክ 4 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ማፍራት በመቻላቸው ነው:: የወረዳው የግብርና ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሌጣ ለገሰ ሽልማቱ ምርትና ምርታማነትን ከፍ ከማድረግ በተጨማሪ የማስፋት ስትራቴጂን አጠናክሮ በማስቀጠል የውድድር መንፈስን ማዳበር እነንዲያስችል  አስረድተዋል:: የሸበዲኖ ወረዳ ደኢህዴን ንዑስ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አበበ ታፈሰ በበኩላቸው የተዘጋጀውን ሽልማት ካበረከቱ በኋላ  እንዳሉት ያገኙትን ውጤት በማስጠበቅ በሚቀጥሉት ጊዜያትም የበለጠ ጠንክረው መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል:: የወረዳው ግብርና ልማት ጽ/ቤት ከአስተዳደሩ  ጋር በመተባበር ባዘጋጀው የሽልማት ስነ ስርዓት 99 ግንባር ቀደም አርሶ አደሮችና 38 የግብርና ባለሙያዎች እንደተሸለሙ ከወረዳው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ያደረሰን መረጃ ያመለክታል:: http://www.smm.gov.et/_Text/04HamTextN604.html

ኣዲሱ የሲዳማ ካርታ ሃዋሳ እና ከቅርብ ኣመታት ወዲህ በሃዋሳ ከተማ ስር የተካተቱትን ኣዳዲስ ክፍለ ከተሞችን ኣያካትትም

Image
ኣዲሱ የሲዳማ  ካርታ ያልተካተቱት የሲዳማ ኣካባቢዎች መካከል ሃዋሳ፤ ከቅርብ ኣመታት ወዲህ በሃዋሳ ከተማ ስር የተካተተውን ኣዲሱን ክፍለ ከተማ ኣቤላ ቱላን ጨምሮ ከከተማ ዙሪያ ያሉትን ዳቶ ኦዳሄ እና ሎቄን የመሳሰሉ ቀበሌዎችን ናቸው። የተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑድርጅቶች ለተለያዩ ጉዳዮች ሲዳማን በተመለከተ እየተጠቀሙ ያሉት ኣዲሱ ካርታ ኣዳዲስ ወረዳዎችን ጨምሮ ከላይ የተጠቀሱትን  የሲዳማ ዞን ኣካባቢዎችን በስተቀር ሁሉንም ወረዳዎችን  ያካተተ ሲሆን የሃዋሳን ከተማና  የኣካባቢውን ቀበሌዎች ኣለማከተቱ በቅርቡ በዞኑ ውስጥ ተነስቶ ለነበረው ህዝባዊ ንቅናቄ መንስኤ ከሆነው የማወያያ ጽሁፍ ጋር መያያዝ ኣለመያያዙ ኣልታወቀም።

የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ ኣመራር ካላ ቤታና ሆጤሳ ሕዝቦች ነጻ የሆነችና የበለጸገች በዘር ያልተከፋፈለች ኢትዮጵያን ለመፍጠር መተባበር አለባቸው ኣሉ፤ ሲኣን በተለያዩ ጉባኤዎች ላይ የሲዳማን ህዝብ በመወከል ላይ ነው

Image
በእንግሊዝ በተካሄደው ለኣዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ጉባኤ የተገኙት ካላ ቤታና ለተሰብሳቢዎች እንደተናገሩት፤ እኛ ኢትዮጵያውያን በየትኛውም መንገድ ቢሆን ለመተባበር መንገድ ማግኘት አለብን። መለስ ባሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያን ለማጥፋት ኢትዮጵያውያንን እየተጠቀመ እንደሆነ ሁሉ እኛ ደግሞ ለመተባበር እርስበርስ መደጋገፍና መተጋገዝ አለብን ያሉት ካላ ቤታና፤   ሕዝቦች ነጻ የሆነችና የበለጸገች በዘር ያልተከፋፈለች ኢትዮጵያን ለመፍጠር መተባበር አለባቸው” ብለዋል።  የጉባኤን ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፦  ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ በእንግሊዝ “የንቅናቄያችን የእንግሊዝ አገር ስብሰባ ስኬታማ ውጤቶች” ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ባለፈው ሳምንት መጠናቀቂያ አካባቢ በእንግሊዝ አገር ሪዲንግ ከተማ በአገራችን ስላለው ”የሰብዓዊ መብት ጥሰት፣ የመሬት ነጠቃ እና የፖለቲካ መብቶች ረገጣ” የንቅናቄያችን የእንግሊዝ ንዑስ (chapter) የሁለት ቀን ስብሰባ አካሂዶ ነበር። በተለይ በስብሰባው መጠናቀቂያ ላይ ከዚህ በፊት ጎራ ለይተው እርስበርስ በዘር፣ በዓላማ፣ በአካሄድ፣ በፕሮግራም ወዘተ የነበሩ የኅብረተሰብ ክፍሎችና ቡድኖች - የትግራይ፣ የአማራ፣ የኦሮሞ፣ የሲዳማ ተወላጆች እንዲሁም ሌሎች የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች፣ ክርስቲያኖች፣ እስላሞች፣ የአንድነት ደጋፊዎች፣ የነጻ አውጪ ግንባሮች፣ የትጥቅ ትግል ደጋፊዎች፣ የሰላማዊ ትግል አራማጆች፣ ወዘተ - በአንድ ቦታ ተገናኝተው ከተወያዩ በኋላ በስብሰባው መጠናቀቂያ ወቅት ሲተቃቀፉ፣ እርስ በርስ በፈገግታ ሲነጋገሩ እንዲሁም የግል መረጃዎቻቸውን ሲለዋወጡ መመልከቱ ብቻ የስብሰባውን ስኬት በግልጽ የሚያሳይ ነበር። ከላይ እንደተገለጸው ንቅናቄያችን ይህንን ስብሰባ ያካሄደበት ዋንኛ ዓላማ