"ሌባ ሲነቃበት እራሱ መልሶ ሌባ ሌባ ብሎ ሰራቂና ጤነኛዉ እንዳይለይ እንደሚያደርግ፡፡ 'ድርጊታቸው/ድብቅ አጀንዳቸው ብቻ ሳይሆን ሊያደርጉ ያሰቡትም ገሀድ ስላወጣና ስለተደረሰባቸው እየተሳደቡ ያሞካሻሉ፡፡ "እንኳንስ ሲሸጡኝ ሲያስማሙኝ አውቃለው፡፡'
በፉቄ ዲሬሞ ከሃዋሳ ሲዳማ ሰሞኑን መንግስት ሲዳማን ርስት አልባ ለማድረግ የሸረበውን ሴራ ለውይይት መቅረቡ መረጃ የደረሰው ሰፊው የሲዳማ ሕዝብ ተቃውሞአቸውን በተለያየ መልኩ ገልጸዋል፤ አሁንም በመግለጽ ላይ ይገኛል ፡፡ ስለሆነም ይህንን ተከትሎ ያልጠበቀው ነገር የገጠመው አቶ ሺህፈራው ሲዳማ በሬ ወልዷል በማለት ሕዝቡን ይቀሰቅሳሉ በማለት ለማስተባበል ሞክሮ ነበር፡፡ ለመሆኑ ሲዳማ በሬ ወልዷል ሜቼ አለ? ለምን ይዋሻል? ከግብር አበሮቹ ጋር በመሆን በሬ ወልዷል ብሎ ለማሳመን በበሬ ቂጥ ላይ እንግደ ልጅ ለጥፎ እንዲሁም ደም ቀብቶ በሬ ወልዷል ስሉን ይህማ በሬ ነው በሬ ወልዶም አያውቅም ልወልድም አይችልም አልን እንጂ፡፡ ለራሱ ተሞኝቶ የሲዳማን ሕዝብ ለማሞኘት ያደረጉትን ጥረት ከሕጻን እስከ አዋቂ ስላወገዘና ድብቅ አጀንዳቸውን ገሀድ ስላወጡ አቶ ሺፈራዉ ሽጉጤ በደቡብ FM ሬዲዮ ሲያስተባብሉና ሲሸፋፍኑ ይባስ ብሎ ሰፊውን የሲዳማን ሕዝብ ሌቦች/ዘራፊዎች ብሎ በሚዲያ ተሳደቡ፡፡"አባት ሲያማ; ልጅ ቢሰማ; ያያል በጠማማ፡፡'እንዲሉ ባለፈው መሬትን ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀው በህዝብ ውይይት መድረኮችም ወቅት በተመሳሳይ ስድብ ዘራፊዎች ተብለን በሚዲያ መሰደባችን ይታወሳል፡፡ ዛሬ ደግሞ ያንኑ ስድባቸውን ሲያጠናክሩ ስራ አጥ ወጣቶች የሲዳማን ስምና ባህል ለማጥፋት የተሰማሩ ዘራፊዎች ሲዳማን የማይወክሉ ናቸው በማለት ለሲዳማ ማንነት፣ ባህልና ታሪክ ተቆርቋሪ ለመምሰል ሞከሩ፡፡ "የሜዳ ላይ ድብብቆሽ ይሉታል ይሄ ነዉ' አንድ ነገር ልብ እንበል ለዛሬው ወቅታዊ አጀንዳቸው ማለትም ሀዋሳን በስብጥር/ በጋራ እናስተዳድር ለሚለው መግቢያ እንዲሆናቸው ባለፈው "የመሬት ወረራ' የሚሉትን አስመልክቶ ሰ