“አፊኒ”
ሚያዝያ መካተቻ ላይ ሐዋሳ ከተማ የዘለቁት የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር አገራችንን እንወቅ ክበብ አባላት ከተፈጥሯዊና ታሪካዊ መስህብ ቦታዎች ጉብኝታቸው ባሻገር ያከናወኑት ዐቢይ ተግባር ችግኝ ተከላ ነበር፡፡ ዘላቂ የቱሪዝም ልማት ተግባራዊነትን ከአካባቢ ጥበቃ አንፃር ዕውን ለማድረግ አንዱ መገለጫው ዛፍ ተከላ እንደመሆኑ፣ የሐዋሳ ከተማ ልዩ መገለጫ የኾነው ሐዋሳ ሐይቅ ህልውናውን ለመጠበቅ በራስጌው ያለውን የታቦር ተራራ ደን ለማልበስ ይረዳ ዘንድ የክበቡ አባላት የችግኝ ተከላውን አካሒደዋል፡፡ ችግኙ የተተከለባት ሐዋሳ ከ52 ዓመት በፊት በልዑል ራስ መንገሻ ሥዩም ስትመሠረት ስሟን ያገኘችው ከሐይቁ መጠርያ ነው፡፡ በሲዳማ ዞን ውስጥ የምትገኘውና ከአዲስ አበባ 273 ኪሎ ሜትር የምትርቀው ሐዋሳ በምዕራብ ሐዋሳ ሐይቅ፣ በደቡብ ሐዋሳ ዙርያና ሸበዲኖ ወረዳዎችን በምሥራቅ ወንዶገነት ወረዳ፣ በሰሜን ሻሸመኔ ይከቧታል፡፡ ከባሕር ወለል 1685 ሜትር ከፍታ ላይ የሚገኘው ሐይቁ የተለያዩ የዓሣ ዝርያዎች እንደአምባዛ ቆሮሶ፣ ቤሩስ ዓይነቶች አሉበት፡፡ አዕዋፋትና የዱር እንስሳትም በአካባቢው ይገኛሉ፡፡ ከአካባቢው ጋር ተስማሚ የሆነ ቱሪዝም ለማስፋፋት፣ ብዝሃ ሕይወትን ለመጠበቅ በአካባቢው የሚገኘውን ታቦር ተራራ በደን መሸፈን አስፈልጓል፡፡ በየጊዜው እንክብካቤ እየተደረገለት በመሆኑም ተራቁቶ የነበረው ታቦር አሁን መልክ እየያዘ ነው፡፡ “ለፍቅር ሐይቁ ውበት ዋስትና የታቦር ገላ በዕጸዋት መሸፈን አለበት” የሚለውን የኅብረተሰቡ አገላለጽ ይበልታ ለመስጠት የተካሔደውን የሚያዝያ 28 ቀን 2004 ዓ.ም. የችግኝ ተከላ ያስተባበረው በሐዋሳ ከተማ የሚገኘው አፊኒ ኢኒሼቲቭ ዴቨሎፕመንት ፎረም ነው፡፡ ችግኝ ተከላውን ሲያስተባብር የነበረውን የፎረሙን ዳይሬክተር አቶ አራርሶ ገረ