Posts

“አፊኒ”

Image
ሚያዝያ መካተቻ ላይ ሐዋሳ ከተማ የዘለቁት የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር አገራችንን እንወቅ ክበብ አባላት ከተፈጥሯዊና ታሪካዊ መስህብ ቦታዎች ጉብኝታቸው ባሻገር ያከናወኑት ዐቢይ ተግባር ችግኝ ተከላ ነበር፡፡ ዘላቂ የቱሪዝም ልማት ተግባራዊነትን ከአካባቢ ጥበቃ አንፃር ዕውን ለማድረግ አንዱ መገለጫው ዛፍ ተከላ እንደመሆኑ፣ የሐዋሳ ከተማ ልዩ መገለጫ የኾነው ሐዋሳ ሐይቅ ህልውናውን ለመጠበቅ በራስጌው ያለውን የታቦር ተራራ ደን ለማልበስ ይረዳ ዘንድ የክበቡ አባላት የችግኝ ተከላውን አካሒደዋል፡፡ ችግኙ የተተከለባት ሐዋሳ ከ52 ዓመት በፊት በልዑል ራስ መንገሻ ሥዩም ስትመሠረት ስሟን ያገኘችው ከሐይቁ መጠርያ ነው፡፡  በሲዳማ ዞን ውስጥ የምትገኘውና ከአዲስ አበባ 273 ኪሎ ሜትር የምትርቀው ሐዋሳ በምዕራብ ሐዋሳ ሐይቅ፣ በደቡብ ሐዋሳ ዙርያና ሸበዲኖ ወረዳዎችን በምሥራቅ ወንዶገነት ወረዳ፣ በሰሜን ሻሸመኔ ይከቧታል፡፡   ከባሕር ወለል 1685 ሜትር ከፍታ ላይ የሚገኘው ሐይቁ የተለያዩ የዓሣ ዝርያዎች እንደአምባዛ ቆሮሶ፣ ቤሩስ ዓይነቶች አሉበት፡፡ አዕዋፋትና የዱር እንስሳትም በአካባቢው ይገኛሉ፡፡ ከአካባቢው ጋር ተስማሚ የሆነ ቱሪዝም ለማስፋፋት፣ ብዝሃ ሕይወትን ለመጠበቅ በአካባቢው የሚገኘውን ታቦር ተራራ በደን መሸፈን አስፈልጓል፡፡ በየጊዜው እንክብካቤ እየተደረገለት በመሆኑም ተራቁቶ የነበረው ታቦር አሁን መልክ እየያዘ ነው፡፡  “ለፍቅር ሐይቁ ውበት ዋስትና የታቦር ገላ በዕጸዋት መሸፈን አለበት” የሚለውን የኅብረተሰቡ አገላለጽ ይበልታ ለመስጠት የተካሔደውን የሚያዝያ 28 ቀን 2004 ዓ.ም. የችግኝ ተከላ ያስተባበረው በሐዋሳ ከተማ የሚገኘው አፊኒ ኢኒሼቲቭ ዴቨሎፕመንት ፎረም ነው፡፡ ችግኝ ተከላውን ሲያስተባብር የነበረውን የፎረሙን ዳይሬክተር አቶ አራርሶ ገረ

የሲዳማ ፓርቲዎች ህብረት ለነፃነት እና ለፊትህ በኢትዮጵያውን ላይ እየደረሰ ያለውን የፖለቲካና የሰብኣዊ መብት ኣፈና ለመዋጋት በኣለም ላይ ያሉ ኢትዮጵያውን ሁሉ ሆ! ብለው እንዲነሱ ጥር ኣቀረበ:: የኢህኣዴግ ቅጥረኞች ሎቄ ላይ በንፁሃን ሲዳማዎች ላይ የፈጸሙት ጭፍጨፋ ኣስረኛው ኣመት በነገው እለት ታስቦ እንደምውል ኣስታውቋል::

New The 10th Anniversary of the Loqqe Massacre of Sidama Civilians Coincides with the Formation of ‘United Sidama Parties for Freedom and Justice’ USPFJ! Press Release by ‘USPFJ’ May 24, 2012 The Loqqe Massacre of the Sidama Civilians, On May 24, 2002, Sidama people of all walks of life staged on a peaceful, nonviolent and  unarmed demonstration claiming their unconditional rights for regional autonomy that was  accorded to the nations whose population is significantly smaller than that of theirs. The  current estimated population of Sidama is over 5.5m. Despite their peaceful demand for  regional autonomy, the demonstrators were met with live ammunitions from the army and the police forces that were assigned to monitor the protest. The regime’s political leadership  from Sidama Zone, Southern Ethiopia Nations and Nationalities and People’s Regional State  up to the central government carefully planned and managed the massacre.  Up to 100 Sidama demonstrators from whom

Moves to twin Bath with Ethiopian city of Hawassa

Image
Bath City  the city of Hawassa A proposal to twin Bath with a city in Ethiopia has been discussed by councillors. The Ethiopian ambassador Berhanu Kebede visited the city this week to meet the Mayor of Bath and discuss the possibility of a twinning arrangement with the city of Hawassa. ​ He was taken to Fairfield House, in Newbridge, which was the home of Ethiopian Emperor Haile Selassie during an exile in the UK between 1936 and 1941. It is this historic link which is the driving force behind the proposal to secure a formal bond between Bath and the African city. Mr Kebede said: "We know this history of this city and how our emperor used to live here and we want to establish a relationship with this historic city. "I have heard from people that the emperor was thankful to the people of Bath during his time of trials and the people of Bath gave him full hospitality and support." He added that there were common links between Hawassa

ይድረስ ለአቶ ኃ/ማርያም ደሳለኝ የኤፌዴሪ ምክትል ጠ/ሚ/ር ና የውጭ ጉዳይ ሚ/ር

መ/ር ቀለሙ ሁነኛው Kelemhun@yahoo.com አቶ ኃ/ማርያም የገፅታዎ ወዘና ሲታይ በእውነቱ ወንበሩ የተመችዎት ይመስላል፡፡ እነ አቶ መለስ ደደቢት በረሀ መሽገው ሲዋጉም ሆነ ደርግን ድል አርገው ቤተመንግስት ሲገቡ ርስዎ በትግል ማህፀን ውስጥ አልተፀነሱም ነበር፡፡ ከወቅቱ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ርቀው ባህር ማዶ በትምህርት ላይ እንደነበሩ ወዳጄ ተመስገን በፍትህ ጋዜጣ ላይ አስነብቦናል፡፡ መቼም እደለኛ ነዎት ይህም ከዕድል ከተቆጠረ፤ ህወሓት /ኢህአዴግ ሕዝብን በብሔረሰብ ከፋፍሎ የመግዛት ፖሊሲውን በመላው አገሪቱ ሲተገብር በወላይታ ብሔር ተወላጅነታችሁ ርስዎና አምባሳደር ተሾመ ቶጋ የአቶ መለስ ቀኝ እጅ በመሆን ብቅ አላችሁ፡፡ የሁለታችሁ ፍፁም ታዛዥነት ለስልጣን ማማ አበቃችሁ፡፡ ክቡር አቶ ኃ/ማርያም የርስዎ መሰላል ግን የሚገርም ነው፡፡ ከስልጣን ወደ ስልጣን ለመሸጋገር ከመፍጠንዎ የሀላፊነትዎ መደራረብ ከበረሀ ጀምሮ ለ17 ዓመታት በፅናት የታገሉት አቶ አዲሱ ለገሠና አቶ ስዩም መስፍን በተናጠል የያዙትን የሥልጣን ቦታ ርስዎ በግልዎ ሲጠቀልሉት ምን አይነት ደስታ ተስማዎት ይሆን? የተደራረበልዎት ሥልጣን የኢህአዴግ ምክትል ሊቀመንበር፣ የኤፌዲሪ ም/ጠ/ሚ/ር፣ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር፣ የሕዳሴ ግድብ አስተባባሪ ብሔራዊ ኮሚቴ የበላይ ጠባቂ የ. . .ድርጅት የቦርድ ሰብሳቢ . . . አቤት የስልጣንዎ ብዛት! መቼም ስልጣንም “የቁጩ” ባይሆን ኖሮ ምድር የሚበቃዎት አይመስለኝም፡፡ አቶ መለስም መተካካት በሚል ለፈጠሯት የሥልጣን ዕድሜ ማራዘሚያቸው ከ2002 ዓ.ም ምርጫ በኋላ ርስዎ ብርሃንዋ በደበዘዘ ባትሪ ተፈልገው ተገኙ፡፡ “ከአብሮ አደግ አትሰደድ” በሚል ውስጠ ሚስጥር የሕይወት መስዋዕትነት እየከፈለ የመጣውን ጀግናውን የ

የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ረቂቅ ፖሊሲ ላይ የሚነጋገር የምክክር መድረክ በአዳማ እየተካሄደ ነው

Image
አዲስ አበባ፣ግንቦት 13 2004 (ዋኢማ)  - የኢትዮጵያን የልማት እቅድ ለማሳካት በተዘጋጀ አዲስ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ረቂቅ ፖሊሲ ላይ የሚነጋገር የምክክር መድረክ በአዳማ እየተካሄደ ነው። የምክክር መድረኩ ላይ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር አቶ ደሴ ዳልኬ እንደገለጹት አዲሱ የሳይንስ ቴክኖሎጂና ፈጠራ ረቂቅ ፖሊሲ የሀገሪቱን ውስን ሀብት በአግባቡ ለመጠቀምና ሊፈጠር የሚችለውን አለም አቀፍ ተጽእኖ ለመቋቋም የሚያግዝ ነው። በውድድር ማእቀፍ ውስጥ በሚካሄደው እንቅስቃሴ ግንባር ቀደም ለመሆን እንደሚያስችልም ተናግረዋል። ፖሊሲው ሀገሪቱ የተያያዘችውን ፈጣንና ዘላቂ የእድገት ጉዞ በአስተማማኝ ሁኔታ ወደፊት በማራመድ ለልማት እቅዱ ተግባራዊነት የሚረዱ የአዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን አጠቃቀም ለማገዝ እንደሚያስችል መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል።