ይድረስ ለአቶ ኃ/ማርያም ደሳለኝ የኤፌዴሪ ምክትል ጠ/ሚ/ር ና የውጭ ጉዳይ ሚ/ር
መ/ር ቀለሙ ሁነኛው Kelemhun@yahoo.com አቶ ኃ/ማርያም የገፅታዎ ወዘና ሲታይ በእውነቱ ወንበሩ የተመችዎት ይመስላል፡፡ እነ አቶ መለስ ደደቢት በረሀ መሽገው ሲዋጉም ሆነ ደርግን ድል አርገው ቤተመንግስት ሲገቡ ርስዎ በትግል ማህፀን ውስጥ አልተፀነሱም ነበር፡፡ ከወቅቱ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ርቀው ባህር ማዶ በትምህርት ላይ እንደነበሩ ወዳጄ ተመስገን በፍትህ ጋዜጣ ላይ አስነብቦናል፡፡ መቼም እደለኛ ነዎት ይህም ከዕድል ከተቆጠረ፤ ህወሓት /ኢህአዴግ ሕዝብን በብሔረሰብ ከፋፍሎ የመግዛት ፖሊሲውን በመላው አገሪቱ ሲተገብር በወላይታ ብሔር ተወላጅነታችሁ ርስዎና አምባሳደር ተሾመ ቶጋ የአቶ መለስ ቀኝ እጅ በመሆን ብቅ አላችሁ፡፡ የሁለታችሁ ፍፁም ታዛዥነት ለስልጣን ማማ አበቃችሁ፡፡ ክቡር አቶ ኃ/ማርያም የርስዎ መሰላል ግን የሚገርም ነው፡፡ ከስልጣን ወደ ስልጣን ለመሸጋገር ከመፍጠንዎ የሀላፊነትዎ መደራረብ ከበረሀ ጀምሮ ለ17 ዓመታት በፅናት የታገሉት አቶ አዲሱ ለገሠና አቶ ስዩም መስፍን በተናጠል የያዙትን የሥልጣን ቦታ ርስዎ በግልዎ ሲጠቀልሉት ምን አይነት ደስታ ተስማዎት ይሆን? የተደራረበልዎት ሥልጣን የኢህአዴግ ምክትል ሊቀመንበር፣ የኤፌዲሪ ም/ጠ/ሚ/ር፣ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር፣ የሕዳሴ ግድብ አስተባባሪ ብሔራዊ ኮሚቴ የበላይ ጠባቂ የ. . .ድርጅት የቦርድ ሰብሳቢ . . . አቤት የስልጣንዎ ብዛት! መቼም ስልጣንም “የቁጩ” ባይሆን ኖሮ ምድር የሚበቃዎት አይመስለኝም፡፡ አቶ መለስም መተካካት በሚል ለፈጠሯት የሥልጣን ዕድሜ ማራዘሚያቸው ከ2002 ዓ.ም ምርጫ በኋላ ርስዎ ብርሃንዋ በደበዘዘ ባትሪ ተፈልገው ተገኙ፡፡ “ከአብሮ አደግ አትሰደድ” በሚል ውስጠ ሚስጥር የሕይወት መስዋዕትነት እየከፈለ የመጣውን ጀግናውን የ