Posts

በሀዋሣ ታቦር ክፍለ ከተማ የፋራ ቀበሌ አስተዳደር የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለአረጋዊያንና ወላጅ አጥ ህፃናት የምሳ ግብዣ አደረገ:

በሀዋሣ ታቦር ክፍለ ከተማ የፋራ ቀበሌ አስተዳደር የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለአረጋዊያንና ወላጅ አጥ ህፃናት የምሳ ግብዣ አደረገ::የቀበሌው ዋና አስተዳዳሪ አቶ በልጉዳ ባሪሳ በዝግጅቱ ላይ እንዳሉት የሁላችንም የጋራ ጠላት የሆነውን ድህነትና ኃላቀርነትን ለማሸነፍ በተሰማራንበት መስክ የበኩላችንን ድርሻ ልንወጣ ይገባል::በቀበሌው ከ47ዐ በላይ አረጋዊያንና ወላጅ አጥ ህፃናት ለምሳ ግብዣው በመጥራት በአሉን በጋራ ማክበር መቻላቸውን አስረድተዋል:: ድጋፍ ያደረጉ ባለሀብቶች በበኩላቸው አመት በዓልን ጠብቆ ለአረጋዊያንና ወላጅ አጥ ህፃናት ከሚደረገው ድጋፍ ባሻገር በዘላቂነት ህይወታቸውን ለመቀየር አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል::የሀዋሣ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ተዋካይ አቶ አየለ ኪአ ቀበሌው እንደዚህ አይነት ዝግጅት በራሱ ተነሳሽነት ማካሄዱ የሚያመሰግነው መሆኑን ገልፀው፤ ሌሎችም አርአያነቱን ሊከተሉ እንደሚገባ አውስተዋል:: የፋራ ቀበሌ ከአመት በዓል ዝግጅቶች ባለፈ የችግረኛ ወገኖችን  ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ስራ እየሰራ መሆኑን ተገልጿል ሲል ባልደረባችን ወንድወሰን ሽመልስ ዘግቧል:: http://www.smm.gov.et/_Text/08MiyaTextN704.html

የሀዋሣ ግብርና ምርመር ማዕከል አዳዲስ የአኩሪ አተርና የባቄላ ዝርያዎችን መልቀቁን አስታወቀ::

የሀዋሣ  ግብርና ምርመር ማዕከል አዳዲስ የአኩሪ አተርና የባቄላ ዝርያዎችን መልቀቁን አስታወቀ::በብሔራዊ የዝሪያዎች አፅዳቂ ኮሚቴ ተገምግሞ የፀደቀው ሁለት የአኩሪ አተርና አንድ የባቄላ ዝርያዎች ሲሆን አስካሁን ከተለቀቁት ከ16 እስከ 21 ቀናት በመቅደም የሚደርሱ ናቸው::ዝርያዎቹ በተዘሩ በአማካኝ ዘጠኝ ቀናት ውስጥ የሚደርሱ ናቸው:: በሽታን የመቋቋም አቅማቸው ከፍተኛ ሲሆን ዝናብ አጠር በሆኑ አካባቢዎች ጭምር ማምራት እንደሚቻል ተገልጿል::ግኝቱ ለአርሶ አደሩ አዋጭ ከመሆኑም በተጨማሪ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግም ከምርምር ማዕከሉ የደረሰን መረጃ ያመለክታል:: http://www.smm.gov.et/_Text/08MiyaTextN904.html

Agricultural Cooperatives and Rural Livelihoods: Evidence from Sidama Ethiopia

Agricultural Cooperatives and Rural Livelihoods: Evidence from Ethiopia Kindie Getnet  affiliation not provided to SSRN Tsegaye ANULLO  affiliation not provided to SSRN Annals of Public and Cooperative Economics, Vol. 83, Issue 2, pp. 181-198, 2012   Abstract:       ABSTRACT:  Agricultural cooperatives are important rural organizations supporting livelihood development and poverty reduction. In recognition of such roles of cooperatives, Ethiopia showed a renewed interest in recent years in promoting cooperative sector development. However, there is lack of a wider and systematic analysis to produce sufficient empirical evidence on the livelihood development and poverty reduction impacts of cooperatives in the country. Using a matching technique on rural household income, saving, agricultural input expenditure and asset accumulation as indicator variables, this paper evaluates the livelihood impact of agricultural cooperatives in  Sidama  zone, Ethiopia. The finding shows tha

Wednesday, April 25, 2012 Colorado State University Signs International Memorandum with Ethiopia's Hawassa University - News & Information - Colorado State University

Image
FORT COLLINS  - Colorado State University signed an international Memorandum of Understanding (MOU) with Ethiopia’s Hawassa University to provide collaborative research and teaching opportunities for faculty and graduate students at the two universities. The MOU was signed in January of this year, and in February, a team of four CSU researchers from the Natural Resource Ecology Laboratory traveled to south-central Ethiopia where they taught short courses in geographic information systems, watershed management, animal nutrition and forest ecology at the Wondo Genet College of Forestry and Natural Resources located off Hawassa’s main campus. Additionally, the team visited potential research sites and met with Hawassa faculty and Peace Corps volunteers. “Hawassa University is very similar to CSU in that both universities are about the same size and offer similar programs, including a veterinary school and a college of natural resources,” said Dave Swift, senior research sc

በሀዋሳ የጎብኚዎች ቁጥርና ከዘርፉ የሚገኘው ገቢ እየጨመረ ነው

Image
ሃዋሳ, ሚያዝያ 16 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - ዜና ትንታኔ በደቡብ ኢትዮጵያ ሰምጥ ሸለቆ የምትገኘው ሀዋሳ ለቱሪስቶች ምቹና ተመራጭ ከተማ እየሆነች መምጣቷን የውጭና የሀገር ውስጥ ጎብኚዎቿና አስተናጋጆቿ ይናገራሉ፡፡ በቅርቡ ሀዋሳ ከተማ ጎራ ብለው የቆዩት ቻይናዊው ሚስተር ጆ ጂን እና ኬንያዊው ሚስተር ኒልሰን ቴምሊ የሀዋሳ ሃይቅ፣የአካባቢው የተፈጥሮና መልከአድራዊ አቀማመጥ፣ሀይቁ ዳር የሚገኘው የሌዊ ሪዞርትና መዝናኛ ፣የህዝቡ እንግዳ አቀባበል ስርአት እንደተመቻቸውና እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል፡፡ የከተማው ንጽህናና ውበት፣በመገንባት ላይ ያሉ አዳዲስ ህንፃዎች ፣ምቹ የመናፈሻ ቦታዎችን ጨምሮ ሀዋሳ ለኑሮ ተስማሚ በመሆኗ ወደፊትም የመዝናኛ ምርጫቸው እንደሆነች ተናግረዋል፡፡ ከአዲስ አበባ ለመዝናናት ወደ አዋሳ ያቀኑት አቶ ኩቲ ኢታይ የተባሉ ኢትዮጵያዊ ማረፊያቸውን ሌዊ ሪዞርት በማድረግ የሀዋሳ ሃይቅ ላይ በዘመናዊ ፈጣን የጀልባ ሽርሽር አሳን በማስገር እንዲሁም የሆቴሉ መስተንግዶና አገልገሎት ምቹ በመሆኑ ትዳር ሲይዙ እዚሁ ለማሳለፍ ምርጫቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በከተማውና አካባቢው ያሉት ተፈጥሮአዊ ታሪካዊና ባህላዊ መስህቦች ለመጎብኘት የሚመጣው የቱሪስት ፍሰትና ከዘርፉ የሚገኘው ገቢ በየዓመቱ እየጨመረ መምጣቱን የሚገልጹት የከተማው ባህል ቱሪዝምና የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ የመረጃና ፕሮሞሽን ባለሙያ ወይዘሮ እታፈራሁ ተምትም ናቸው፡፡ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ 97 ሺህ 187 የውጭና የሀገር ውስጥ ቱሪስቶች ተስተናግደው ከ22 ሚልዮን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል ፡፡ ከጎብኚዎቹም መካከል ከ21 ሺህ በላይ የውጭ ቱሪስቶች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በጎብኚዎች ብዛ