Posts

በሀዋሳ የጎብኚዎች ቁጥርና ከዘርፉ የሚገኘው ገቢ እየጨመረ ነው

Image
ሃዋሳ, ሚያዝያ 16 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - ዜና ትንታኔ በደቡብ ኢትዮጵያ ሰምጥ ሸለቆ የምትገኘው ሀዋሳ ለቱሪስቶች ምቹና ተመራጭ ከተማ እየሆነች መምጣቷን የውጭና የሀገር ውስጥ ጎብኚዎቿና አስተናጋጆቿ ይናገራሉ፡፡ በቅርቡ ሀዋሳ ከተማ ጎራ ብለው የቆዩት ቻይናዊው ሚስተር ጆ ጂን እና ኬንያዊው ሚስተር ኒልሰን ቴምሊ የሀዋሳ ሃይቅ፣የአካባቢው የተፈጥሮና መልከአድራዊ አቀማመጥ፣ሀይቁ ዳር የሚገኘው የሌዊ ሪዞርትና መዝናኛ ፣የህዝቡ እንግዳ አቀባበል ስርአት እንደተመቻቸውና እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል፡፡ የከተማው ንጽህናና ውበት፣በመገንባት ላይ ያሉ አዳዲስ ህንፃዎች ፣ምቹ የመናፈሻ ቦታዎችን ጨምሮ ሀዋሳ ለኑሮ ተስማሚ በመሆኗ ወደፊትም የመዝናኛ ምርጫቸው እንደሆነች ተናግረዋል፡፡ ከአዲስ አበባ ለመዝናናት ወደ አዋሳ ያቀኑት አቶ ኩቲ ኢታይ የተባሉ ኢትዮጵያዊ ማረፊያቸውን ሌዊ ሪዞርት በማድረግ የሀዋሳ ሃይቅ ላይ በዘመናዊ ፈጣን የጀልባ ሽርሽር አሳን በማስገር እንዲሁም የሆቴሉ መስተንግዶና አገልገሎት ምቹ በመሆኑ ትዳር ሲይዙ እዚሁ ለማሳለፍ ምርጫቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በከተማውና አካባቢው ያሉት ተፈጥሮአዊ ታሪካዊና ባህላዊ መስህቦች ለመጎብኘት የሚመጣው የቱሪስት ፍሰትና ከዘርፉ የሚገኘው ገቢ በየዓመቱ እየጨመረ መምጣቱን የሚገልጹት የከተማው ባህል ቱሪዝምና የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ የመረጃና ፕሮሞሽን ባለሙያ ወይዘሮ እታፈራሁ ተምትም ናቸው፡፡ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ 97 ሺህ 187 የውጭና የሀገር ውስጥ ቱሪስቶች ተስተናግደው ከ22 ሚልዮን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል ፡፡ ከጎብኚዎቹም መካከል ከ21 ሺህ በላይ የውጭ ቱሪስቶች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በጎብኚዎች ብዛ

Over 153,000 People Receive VCT Service in Sidama

Hawassa, 14 April 2012 (allAfrica)  — More than 153,  people  have received HIV and AIDS Voluntary Counseling and blood Testing (VCT) in Sidama Zone over the past seven months, the zonal health department said. Health Promotion and Disease Preventions Process owner coordinator Yohannes Latamo told ENA that more than 80,000 of them are women. He said the department is working with government and NGOs to expand VCT service to reach out more community. Some 520 people have found to be positive, he said. Following the establishment of HIV and AIDS fund in government offices care and support service is being offered to 39 people living with HIV and AIDS, he said. He said government offices have also allocated two percent of their budget each for HIV and AIDS prevention and control activities. With this fund, 21 people living with HIV and AIDS are taking Anti-Retroviral Treatment and more than 5,000 orphaned and vulnerable children are provided shelter, food and  educational m

የሃዋሳ ስታዲዬም በ548 ሚሊዮን ብር ወጪ የግንባታ ስራው ተጀመረ

የደቡብ ክልል መንግሥት ነዋሪዎቹ ለሕዳሴው ግድብ ግንባታ ገንዘብ እያዋጡ በመሆኑ ላለማስጨነቅ ሲል በራሱ ወጭ የአዲስ ስታዲየም ግንባታ አስጀመረ፡፡ ክልሉ ለስታዲየሙና ለተያያዥ ግንባታዎች ትናንት ሐሙስ ሚያዝያ 11 ቀን 2004 ዓ.ም. ሳትኮን ኮንስትራክሽን ኩባንያ በ548 ሚሊዮን ብር እንዲገነባለት ውል ተፈራርሟል፡፡ ከዚህ በጀት ውስጥ 80 ሚሊዮኑን በዚህ የበጀት ዓመት ለሚሠሩ ሥራዎች የሚውል ሲሆን፣ ይህንን ጨምሮ በ2005 በጀት ዓመትም ለሥራው የሚያስፈልገውን ገንዘብ የሚመድበው ክልሉ ነው፡፡ ይህ የተወሰነው ሐዋሳ ከተማ ላይ ስታዲየሙን ጨምሮ የሚገነባውን ግዙፍ የስፖርት ኮምፕሌክስ እንዲያሠራ የተሰየመው ምክር ቤት ከክልሉ መንግሥት ጋር ከመከረ በኋላ መሆኑ ታውቋል፡፡ የስፖርት ኮምፕሌክስ ግንባታ ፕሮጀክት ማስተባበርያ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሰፋ አመሎ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በ2004 እና በ2005 በጀት ዓመት ክልሉ ከራሱ ካዝና እየመደበ ያሠራል፡፡ በ2006 በጀት ዓመት ሕዝብ ለግንባታው አስተዋጽዖ እንዲያደርግ ይጠይቃል ሲሉ አስረድተዋል፡፡ ሥራውን ሐሙስ ተረክቦ በዕለቱ ቁፋሮ የጀመረው ሳትኮን ኮንስትራክሽን ይህንን ፕሮጀክት ለማሸነፍ ከስምንት ኮንስትራክሽን ኩባንያዎች ጋር ተወዳድሯል፡፡ ከስምንቱ ውስጥ ሦስቱ በቴክኒካል ጨረታ ሲወድቁ፣ አምስቱ ጨረታውን አልፈው በፋይናንስ ጨረታ ተወዳድረዋል፡፡ ከእነዚህ ኩባንያዎች ውስጥ ሳትኮንን ጨምሮ አፍሮ ጽዮን ኮንስትራክሽን፣ ሚድሮክ ኮንስትራክሽንና ቫርኔሮ ይገኙበታል፡፡ ከአምስቱ የኮንስትራክሽን ኩባንያዎች ውስጥ ዝቅተኛውን 548 ሚሊዮን ብር ለመጀመርያው ዙር የስታዲዮም ግንባታ በማቅረብ ሳትኮን አሸንፏል፡፡ ከፍተኛ የሆነውን የጨረታ ገንዘብ 564 ሚሊዮን ብር ያቀረበው ቫርኔሮ ሲሆን፣ ሦስቱ ኮንስትራክሽን

ለወላጅ አጥና ለችግር የተጋለጡ ህፃናት ሁሉ አቀፍ ድጋፍ ሊደረግላቸው እንደሚገባ ተገለፀ:

ለወላጅ አጥና ለችግር የተጋለጡ ህፃናት ሁሉ አቀፍ ድጋፍ ሊደረግላቸው እንደሚገባ ተገለፀ::በሀዋሣ ከተማ የምሥራቅ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የከፍተኛ ሁለት ዐ3 ቀበሌ መረዳጃ እድርና ልማት ማህበር ከእየሩሳሌም የህፃናትና ማህበረሰብ ልማት ከሳውዲን ተራድኦ ድርጅት ኘሮጀክት ጋር በመተባበር ለ145 ወላጅ አጥና ችግረኛ ህፃናት የፋሲካን በዓል ምክንያት በማድረግ የተለያዩ የአልባሳት ድጋፍ አድርጓል:: የኢየሩሳሌም የህፃናትና ማህበረሰብ ልማት ድርጅት የሀዋሣ ቅርንጫፍ ሥራ አስያኪጅ አቶ ማስረሻ ክብረት እንዳሉት ህፃናቱ ቀደም ሲል የትምህርት ፣ የጤናና የስነ ልቦና ድጋፍ ሲሰጣቸው የቆዩ ናቸው::ከፍተኛ ሁለት ዐ3 መረዳጃ እድርና ልማት ማህበር ከድርጅታቸው ጋር በመተባበር የሚያደርግላቸውን ድጋፍ በመጠቀም ህፃናቱ በትምህርታቸው ውጤታማ ለመሆን መስራት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል:: የምሥራቅ ክፍለ ከተማ አስተዳዳሪ ወይዘሮ ዘውዲቱ ገ/መስቀል በበኩላቸው የመረዳጃ እድርና ልማት ማህበሩ ከረጂ ድርጅቶች ጋር በመተባበር  በክፍለ ከተማው በዓላትን ምክንያት በማድረግ በየዓመቱ ለወላጅ አጥና ችግርተኛ ህፃናት የተለያዩ ድርጋፎችን  እንደሚያደርግ ተናግረዋል:: የአሁኑ ተረጂ ህፃናት በሚደረግላቸው ድጋፍ ተግተው ከተማሩ የነገይቱ አገር ተረካቢና የተሻለ ዜና መሆን እንደሚችሉም ጠቁመዋል፡፡ ባልደረባችን ጌታሁን አንጭሶ እንደዘገበው::

Hawassa constructing 40 mln. Birr worth cultural centre

Image
Hawassa, April 21, 2012 (Hawassa) - Construction of a multi-purpose hall cultural centre is underway in Hawassa town of South Ethiopia Peoples State at a cost of close to 40 million Birr, the town municipality said. Municipality deputy manager, Biru Wolde told ENA that the center, which would be finalized in the next Ethiopian budget year would accommodate 1,700 guests at a time. He said the centre which houses conference hall, theater and art gallery, among others would help conserve historical and cultural heritages of the region. The construction has created dozens of jobs. The regional government and the municipality have covered the construction cost of the centre.