Posts

የሃዋሳ ስታዲዬም በ548 ሚሊዮን ብር ወጪ የግንባታ ስራው ተጀመረ

የደቡብ ክልል መንግሥት ነዋሪዎቹ ለሕዳሴው ግድብ ግንባታ ገንዘብ እያዋጡ በመሆኑ ላለማስጨነቅ ሲል በራሱ ወጭ የአዲስ ስታዲየም ግንባታ አስጀመረ፡፡ ክልሉ ለስታዲየሙና ለተያያዥ ግንባታዎች ትናንት ሐሙስ ሚያዝያ 11 ቀን 2004 ዓ.ም. ሳትኮን ኮንስትራክሽን ኩባንያ በ548 ሚሊዮን ብር እንዲገነባለት ውል ተፈራርሟል፡፡ ከዚህ በጀት ውስጥ 80 ሚሊዮኑን በዚህ የበጀት ዓመት ለሚሠሩ ሥራዎች የሚውል ሲሆን፣ ይህንን ጨምሮ በ2005 በጀት ዓመትም ለሥራው የሚያስፈልገውን ገንዘብ የሚመድበው ክልሉ ነው፡፡ ይህ የተወሰነው ሐዋሳ ከተማ ላይ ስታዲየሙን ጨምሮ የሚገነባውን ግዙፍ የስፖርት ኮምፕሌክስ እንዲያሠራ የተሰየመው ምክር ቤት ከክልሉ መንግሥት ጋር ከመከረ በኋላ መሆኑ ታውቋል፡፡ የስፖርት ኮምፕሌክስ ግንባታ ፕሮጀክት ማስተባበርያ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሰፋ አመሎ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በ2004 እና በ2005 በጀት ዓመት ክልሉ ከራሱ ካዝና እየመደበ ያሠራል፡፡ በ2006 በጀት ዓመት ሕዝብ ለግንባታው አስተዋጽዖ እንዲያደርግ ይጠይቃል ሲሉ አስረድተዋል፡፡ ሥራውን ሐሙስ ተረክቦ በዕለቱ ቁፋሮ የጀመረው ሳትኮን ኮንስትራክሽን ይህንን ፕሮጀክት ለማሸነፍ ከስምንት ኮንስትራክሽን ኩባንያዎች ጋር ተወዳድሯል፡፡ ከስምንቱ ውስጥ ሦስቱ በቴክኒካል ጨረታ ሲወድቁ፣ አምስቱ ጨረታውን አልፈው በፋይናንስ ጨረታ ተወዳድረዋል፡፡ ከእነዚህ ኩባንያዎች ውስጥ ሳትኮንን ጨምሮ አፍሮ ጽዮን ኮንስትራክሽን፣ ሚድሮክ ኮንስትራክሽንና ቫርኔሮ ይገኙበታል፡፡ ከአምስቱ የኮንስትራክሽን ኩባንያዎች ውስጥ ዝቅተኛውን 548 ሚሊዮን ብር ለመጀመርያው ዙር የስታዲዮም ግንባታ በማቅረብ ሳትኮን አሸንፏል፡፡ ከፍተኛ የሆነውን የጨረታ ገንዘብ 564 ሚሊዮን ብር ያቀረበው ቫርኔሮ ሲሆን፣ ሦስቱ ኮንስትራክሽን

ለወላጅ አጥና ለችግር የተጋለጡ ህፃናት ሁሉ አቀፍ ድጋፍ ሊደረግላቸው እንደሚገባ ተገለፀ:

ለወላጅ አጥና ለችግር የተጋለጡ ህፃናት ሁሉ አቀፍ ድጋፍ ሊደረግላቸው እንደሚገባ ተገለፀ::በሀዋሣ ከተማ የምሥራቅ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የከፍተኛ ሁለት ዐ3 ቀበሌ መረዳጃ እድርና ልማት ማህበር ከእየሩሳሌም የህፃናትና ማህበረሰብ ልማት ከሳውዲን ተራድኦ ድርጅት ኘሮጀክት ጋር በመተባበር ለ145 ወላጅ አጥና ችግረኛ ህፃናት የፋሲካን በዓል ምክንያት በማድረግ የተለያዩ የአልባሳት ድጋፍ አድርጓል:: የኢየሩሳሌም የህፃናትና ማህበረሰብ ልማት ድርጅት የሀዋሣ ቅርንጫፍ ሥራ አስያኪጅ አቶ ማስረሻ ክብረት እንዳሉት ህፃናቱ ቀደም ሲል የትምህርት ፣ የጤናና የስነ ልቦና ድጋፍ ሲሰጣቸው የቆዩ ናቸው::ከፍተኛ ሁለት ዐ3 መረዳጃ እድርና ልማት ማህበር ከድርጅታቸው ጋር በመተባበር የሚያደርግላቸውን ድጋፍ በመጠቀም ህፃናቱ በትምህርታቸው ውጤታማ ለመሆን መስራት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል:: የምሥራቅ ክፍለ ከተማ አስተዳዳሪ ወይዘሮ ዘውዲቱ ገ/መስቀል በበኩላቸው የመረዳጃ እድርና ልማት ማህበሩ ከረጂ ድርጅቶች ጋር በመተባበር  በክፍለ ከተማው በዓላትን ምክንያት በማድረግ በየዓመቱ ለወላጅ አጥና ችግርተኛ ህፃናት የተለያዩ ድርጋፎችን  እንደሚያደርግ ተናግረዋል:: የአሁኑ ተረጂ ህፃናት በሚደረግላቸው ድጋፍ ተግተው ከተማሩ የነገይቱ አገር ተረካቢና የተሻለ ዜና መሆን እንደሚችሉም ጠቁመዋል፡፡ ባልደረባችን ጌታሁን አንጭሶ እንደዘገበው::

Hawassa constructing 40 mln. Birr worth cultural centre

Image
Hawassa, April 21, 2012 (Hawassa) - Construction of a multi-purpose hall cultural centre is underway in Hawassa town of South Ethiopia Peoples State at a cost of close to 40 million Birr, the town municipality said. Municipality deputy manager, Biru Wolde told ENA that the center, which would be finalized in the next Ethiopian budget year would accommodate 1,700 guests at a time. He said the centre which houses conference hall, theater and art gallery, among others would help conserve historical and cultural heritages of the region. The construction has created dozens of jobs. The regional government and the municipality have covered the construction cost of the centre.

Sidama Libration Front -የሲዳማ ነፃ ኣውጭ ድርጅት ኣላማዎች እና በሲዳማ ወቅታዊ ፖለቲካዊ ሁኔታ ላይ ከድርጅቱ መሪ ከኣቶ ቤታና ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ

Image
Seife Nebelbal Radio, April 20, 2012, Interview: Asli Oromo and Sidama Liberation leader Kaala Betana የሲዳማ ነፃ ኣውጭ ድርጅት ኣላማዎች እና በሲዳማ ወቅታዊ ፖለቲካዊ ሁኔታ ላይ ከድርጅቱ መሪ ከኣቶ ቤታና ጋር  የተደረገ ቃለ ምልልስ ከ 24 ደቂቃ ጀምረው ያዳምጡ::

መድኃኒትና ንብረት የዘረፉ ክስ ተመሠረተባቸው

Image
ፈንድ አቅርቦት ኤጀንሲ የሃዋሳ ቅርንጫፍ የጥበቃ ሠራተኛ የነበረው ግለሰብና ሌሎች ስድስት ግለሰቦች በመመሳጠር ከኤጀንሲው የመድኃኒት ማቆያ መጋዘን ውስጥ ከ1ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት መድኃኒት በመዝረፍ በከባድ የእምነት ማጉደል የሙስና ወንጀል ተከሰሱ። የፌዴራል የሥነ ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በግለሰቦቹ ላይ የመሠረተው ክስ እንደሚያመለክተው የኤጀንሲው የጥበቃ ሠራተኛ የነበረ 1ኛ ተከሳሽ የመንግሥትን ንብረት እንዲጠብቅ የተሰጠውን ኃላፊነት ወደጎን በመተው ተገቢ ያልሆነ ጥቅም ለራሱ እና ለግብረ አበሮቹ ለማስገኘት በማሰብ ለሕዝብ አገልግሎት ይውሉ የነበሩትን መድኃኒቶች፣ ኬሚካሎች፣ የሕክምና መሣሪያዎች እንዲዘረፉ በማድረጉ ከባድ የእምነት ማጉደል የሙስና ወንጀል ፈጽሟል። የኤጀንሲው ሠራተኞች ያልሆኑት ከ2ኛ እስከ 6ኛ ያሉ ተከሳሾች ከ1ኛ ተከሳሽ ጋር ተመሳጥረው መድኃኒት የተከማቸበትን መጋዘን ቁልፍ በመስበር መድኃኒቱ የሚጫንበትን ተሽከርካሪ በማዘጋጀት መድኃኒቱን ከመጋዘን አውጥተው በመጫን እንዲሁም መድኃኒቱ የሚራገፍበትን ቦታ በማመቻቸት በወንጀሉ ድርጊት ሙሉ ተሳታፊና በወንጀሉ የተገኘውን ውጤት ተካፋይ መሆናቸውን የክስ መዝገቡ ያስረዳል። 7ኛ ተከሳሽ የሆነው የኤጀንሲው የጥበቃ ተከሳሽ ዘረፋው በተፈጸመበት ዕለት ተረኝነቱን ሳይጠብቅና የሙያ ግዴታውን በአግባቡ ሳይፈጽም ሌሊቱን ጥበቃ ላይ የነበረ በማስመሰል በሰዓት መቆጣጠሪያ ላይ በመፈረሙ በፈጸመው የሥራ ኃላፊነትን ባለመወጣት የሙስና ወንጀል ተከስሷል። በአጠቃላይ ሁሉም ተከሳሾች በግብረአበርነት በፈጸሙት የሙስና ወንጀል ግምቱ 1ነጥብ7ሚሊዮን ብር የሚያወጣ መድኃኒት ኬሚካሎች ሰፕላይስ እና የሕክምና መሣሪያዎችን በመዝረፋቸው ኮሚሽኑ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ወንጀል ች