Posts

በሲዳማ ዞን አሮሬሳ ወረዳ በቀበሌ ተደራሽ መንገድ ግንባታ ከ33 ኪሎ ሜትር በላይ መንገድ እየተሰራ ነው፡

በሲዳማ ዞን አሮሬሳ ወረዳ በቀበሌ ተደራሽ መንገድ ግንባታ ከ33 ኪሎ ሜትር በላይ መንገድ እየተሰራ ነው፡፡በወረዳው በመገንባትና በመጠገን ላይ የሚገኙት መንገዶች ሁሉም ቀበሌያት ከወረዳዋ ዋና ከተማ የሚያገናኙ ናቸው፡፡የወረዳው የመንገዶችና ትራንስፖርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ ተወካይ አቶ ድንቅነህ አለማየሁ ግንባታዎቹ የህዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት ተጠቃሚነትን ወደ ተሻለ ደረጃ ያደርሱታል፡፡ በተለይ ወረዳውን ከኦሮሚያ ክልል የሚያገናኘው ሔማ የተባለው የ18 ኪሎ ሜትር መንገድ ሲጠናቀቅ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታው የላቀ እንደሆነ መግለፃቸውንም የሲዳማ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ዘግቧል፡፡ http://www.smm.gov.et/_Text/25MegTextN504.html

በህብረሰቡ ጤና ላይ ጉዳት በማያደርስ መልኩ የደረቅና ፈሳሽ የማስወገጃ ሥራ በተጠናከረ መልኩ እየሠራ መሆኑን የሀዋሣ ከተማ ማዘጋጃ ቤት አስታወቀ፡፡

በህብረሰቡ ጤና ላይ ጉዳት በማያደርስ መልኩ የደረቅና ፈሳሽ የማስወገጃ ሥራ በተጠናከረ መልኩ እየሠራ መሆኑን የሀዋሣ ከተማ ማዘጋጃ ቤት አስታወቀች፡፡ከአሁን በፊት በከተማው የነበረው የደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ ሥርዓት በህብረተሰቡ ጤና ላይ ጉዳት የሚያደርስ ሲሆን አዲስ አሠራር ችግሩን መቅረፍ እንደሚችል ነው ነዋሪዎቹ የተናገሩት፡፡ ማዘጋጃ ቤቱ አሠራሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ጠቁመዋል፡፡በአገራችን አብዛኞቹ በሽታዎች የሚከሰቱት በግልና በአካባቢ ንጽህና ጉድለት ነው፡፡ችግሩን በቀላሉ መቅረፍ እንዲቻል  በደየደረጃው የጤና ኤክስቴንሽን ኘሮግራም ተዘርግቶ የግልና የአካባቢ ንጽህና አጠባበቅ ዙሪያ ትምህርት በመስጠት በንጽህና ጉድለት የሚመጡ በሽታዎችን አስቀድሞ መከላከል እየተቻለ ነው፡፡ ቀደም ሲል በሀዋሣ ከተማ የነበረው የደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ ቆሻሻው በሚጣልባቸው አካባቢዎች በሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ይፈጥር እንደነበር ነው ነዋሪዎቹ የሚናገሩት፡፡በአሁኑ ሰዓት ከየአቅጣጫው የሚሰበሰበው ደረቅ ቆሻሻ በማጠራቀሚያ ቦታ ላይ ተከማችቶ ሳይቆይ ከአፈር ጋር የማደባለቅ ሥራ በመሠራቱ በአካባቢው የሚፈጠረው መጥፎ ሽታ እየቀነሰ መምጣቱን ነው አንዳንዱቹ የሚያስረዱት፡፡ የከተማው ማዘጋጃ ቤት ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ብሩ ወልዴ በበኩላቸው የደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ ሥርዓቱ በህብረተሰቡ ጤናና  አካባቢ ላይ ጉዳት በማያደርስ መልኩ ጥናት ተደርጐበት ወደ ሥራ መገባቱን ገልፀዋል፡፡ከደረቅ ቆሻሻ ጋር ተቀላቅለው የሚመጡ ኘላስቲኮች በንፋስ እየተነሱ አካባቢን እንዳይበክሉ ለማድረግ ለብቻ ተለቅመው ተመልሰው አገልግሎት ላይ የሚውሉበትን ሁኔታ በማመቻቸት ላይ እንደሚገኙም ጠቁመዋል፡፡ ከተለያዩ አካባቢዎች በአህያ ጋሪ የሚጓጓዘው ደረቅ ቆሻሻ በከተማ ውስጥ የሚ

የዳራ ወረዳ ውና፣ ማዕድንና ኢነርጂ ጽህፈት ቤት ከ2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ህብረተሰቡን ንፁህ የመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ መንግስታዊ ካልሆነ ድርጅት ጋር በመቀናጀት እየሰራ መሆኑን ገለፀ፡፡

የዳራ ወረዳ ውና፣ ማዕድንና ኢነርጂ ጽህፈት ቤት ከ2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ህብረተሰቡን ንፁህ የመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ መንግስታዊ ካልሆነ ድርጅት ጋር በመቀናጀት እየሰራ መሆኑን ገለፀ ፡፡ የጽህፈት ቤቱ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና የተቋማት አስተዳደር ሥራ ሂደት አስተባባሪ ተወካይ አቶ ባንታየሁ ጉዲሳ አንደገለፁት በንፁህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና ሳኒቴሽን ኘሮግራም እቅድ ከተያዙት 17 ምንጮች የ12ቱ ግንባታ 87 በመቶ ተጠናቋል ፡፡ የግንባታው ወጪም 85 በመቶ ትንሳኤና ብርሃን በተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት የሚሸፈን ሲሆን 15 በመቶ በወረዳው በጀት ይሸፈናል ፡፡ ግንባታው ሲጠናቀቅ የወረዳው የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋን 38 ነጥብ 8 በመቶ ይደርሳል ማለታቸውን የወረዳው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጽህፈት ቤት ዘግቧል ፡፡

በሲዳማ ዞን ቦርቻ ወረዳ በግማሽ የበጀት ዓመት በአፈፃፀማቸው የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ 6 ቀበሌየት የማበረታቻ ሽልማት ተሰጠ፡፡

በሲዳማ ዞን ቦርቻ ወረዳ በግማሽ የበጀት ዓመት በአፈፃፀማቸው የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ 6 ቀበሌየት የማበረታቻ ሽልማት ተሰጠ፡፡የወረዳው ምክር ቤት በ6 ወር የእቅድ አፈፃፀም ዙሪያ ከቀበሌ አፈ ጉባኤዎች፣ ሊቀነ መናብርትና ሥራ አስኪያጆች ጋር ሰሞኑን ውይይት አካሂዷል፡፡ የምክር ቤቱ ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ በላይነሽ ብዙነህ እንደተናገሩት ቀበሌያቱ ሊሸለሙ የቻሉት ደረጃውን የጠበቀ የቀበሌ ምክር ቤት በማቋቋም የህብረተሰቡን ፍላጎት መሠረት ያደረጉ ፈጣን አገልግሎት መስጠት በመቻላቸው ነው፡፡ ቀበሌያቱ ለተለያዩ የልማት ሥራዎት የቅርብ ድጋፍና ክትትል በማድረግ እንዲሁም በየወሩ የሸንጎ አባላት ጉባኤ በማካሄድ ለወረዳ ምክር ቤት ወቅቱን የጠበቀ ሪፖርት በማቅረባቸው ጭምር መሆኑንም አስረድተዋል፡፡የወረዳው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዘግቧል፡፡

የሀዋሳ ከተማን ጽዳትና ውበት በመጠበቅ የቱሪዝም ማዕከል ለማደረግ የድርሻቸውን እንደሚወጡ ነዋሪዎች ገለጹ

  የሀዋሳ ከተማን ጽዳትና ውበት በመጠበቅ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ነዋሪዎች ከከተማው አስተዳደሩ ጋር ተባብረው እንደሚሰሩ አስታወቁ፡፡ የፋሲካን በዓል ምክንያት በማድረግ የመንግስት ሰራተኞችና የንግዱ ማህበረሰብ ጨምሮ በከተማው ስምንቱም ክፍለ ከተሞች የሚገኙ ነዋሪዎች የተሳተፉበት የጽዳትና የተተከሉ የዛፍ ችግኞችን የመንከባከብ የስራ ዘመቻ ትናንት ተካሄዷል፡፡ የከተማው አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዮናስ ዮሴፍ በየክፍለ ከተማው ተዘዋውረው በስራው የተሳተፉትን ነዋሪዎች አበረታትዋል፡፡ "እያንዳንዱ አካባቢውን ካጸዳ ከተማዋ የጸዳች ትሆናለች" በሚል መርህ ትናንት ለግማሽ ቀን በተካሄደው የስራ ዘመቻ ከተሳተፉት መካከል በባህል አዳራሽ ክፍለ ከተማ የሀረር ቀበሌ ነዋሪው ወጣት ሙሉቀን አለማየሁ በሰጠው አስተያየት አካባቢቸውን ከቆሻሻና ከብክለት ለመከለካል ከሰፈር ጓደኞቹና ነዋሪው ጋር በራሳቸው ተነሳሽነት የጽዳት ዘመቻውን በዓሉን ምክንያት በማድረግ ብቻ ሳይሆን በቋሚነት በየሳምንቱ እየሰሩ መሆናቸውን ገልጿል፡፡ አካባቢያቸውን ከፍሳሽና ከደረቅ ቆሻሻ ማዕዳት ለጤናቸው ብሎም ለሀዋሳ ውበትና አረንጓዴ ልማት የላቀ አስተዋጾኦ እንዳለው በመገንዘብ በቀጣይም ከከተማው አስተዳደርና ማዘጋጃ ቤት ጋር በመተባበር የበኩላቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ የዚሁ ክፍለ ከተማና ቀበሌ ነዋሪ ወይዘሮ አሰለፈች በቀለ በበኩላቸው ሀዋሳ ያላትን ጽዳትና ውበት ለማስጠበቅ ጽዳትን ከቤታቸውና ከመንደራቸው በመጀመር እየሰሩ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ የመሃል ክፍለ ከተማ ቀበሌ 02 ነዋሪ ወይዘሮ እናኑ መዘምር በሰጡት አስተያየት ጽዳት ለጤንነትና ለከተማ ውበት ወሣኝ መሆኑን በመረዳት ቆሻሻን ከአካባ