Posts

የቡና ዋጋ ወሰን ሙሉ ለሙሉ ተነሳ

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ የቡና መገበያያ  የዋጋ ወሰንን ከትናንት በስቲያ ገበያ መዝጊያ ዋጋ አኳያ ወደ ላይና ወደ ታች የአምስት በመቶ ጭማሪና ቅናሽ እንዲያሳይ በማድረግ ሲያገበያይበት የነበረውን አሠራር ላልተወሰነ ጊዜ ማንሳቱን አስታወቀ፡፡ የምርት ገበያው ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር እሌኒ ገብረ መድኅን ለሪፖርተር እንዳስታወቁት፣ የዋጋውን ወሰን ማንሳት ያስፈለገው በኒውዮርክ ዓለም አቀፍ ገበያ ከጊዜ ወደጊዜ እያሽቆለቆለ የመጣው የቡና ዋጋ፣ ባለፈው ሐሙስ ዕለት በፓውንድ (ግማሽ ኪሎ ገደማ) አንድ ዶላር ከሰባ አምስት ሳንቲም የሆነ ዝቅተኛ ዋጋ በማስመዝገቡ የዋጋ ወሰኑን ሙሉ ለሙሉ ማንሳት አስፈልጓል፡፡ የዓለም የቡና ዋጋ እስኪስተካከል ድረስ የዋጋ ወሰኑ ሙሉ ለሙሉ ተነስቶ እንደሚቆይ የገለጹት ዶክተር እሌኒ፣ የአገር ውስጥ አቅራቢዎች የቡና ዋጋ መው ረዱን የማይቀበሉት ከዚህ ቀደም የተሻለ ዋጋ ለማግኘት አስበው በእጃቸው ያቆዩት ቡና ይበልጥ ዋጋው ሲወርድ ለኪሳራ ስለሚያጋልጣቸው ነው ብለዋል፡፡ ይህም ሆኖ አቅራቢዎች በግድ ሽጡ እንዳልተባሉ ገልጸው፣ ምርቱን በእጃቸው ከማቆየት ይልቅ ግን እንዲህ ያለ ያልታሰበ የዋጋ ማሽቆልቆል እንዳይከሰት በእጃቸው ያለውን ቡና ቶሎ ለገበያ እንዲያቀርቡ መክረዋል፡፡ ከሦስት ወራት በፊት የቡና ዋጋ እስኪጨምር ድረስ ምርቱን በእጃቸው ይዘው ሲጠባበቁ የነበሩ አቅራቢዎች የዋጋው መውረድ እንደጎዳቸው ገልጸው፣ አምና በፓውንድ ሦስት ዶላር ያወጣ የነበረው ቡና ባለፈው ወር ወደ ሁለት ዶላር ሊወርድ መቻሉን አስረድተዋል፡፡ በዚህ ያላቆመው የዋጋ ማሽቆልቆል ከሁለት ሳምንት በፊት የኒውዮርክ ገበያ ዋጋው ወደ አንድ ዶላር ከዘጠና ሊወርድ መቻሉን፣ ባለፈው ሐሙስ ደግሞ ብሶበት አንድ ዶላር ከሰባ አምስት ሳንቲም ማውጣቱን ይገልጻሉ፡፡  በአንፃሩ በምርት

በሐዋሳ በተነሳው የእሳት አደጋ ንብረት አወደመ: በሐዋሳ ከተማ የንግድ ተቋማት ባለንብረቶች: ከኢንሹራንስ ይልቅ ማኅበራዊ ተራድኦን የሚመርጡ መሆናቸው ተነገረ

Image
 በአደጋው የከተማው አስተዳደር እሳት አደጋ መከላከል አቅም ተፈትሿል መጋቢት 9 ቀን 2004 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ገደማ በሐዋሳ ከተማ ፒያሳ አካባቢ በሁለት መደብሮች የተነሳው እሳት ንብረት አወደመ:: ወደ ክብሩ ሆስፒታል መሄጃ ላይ እየሩሳሌም የጨርቃ ጨርቅ መደብርንና አጠገቡ ያለው ጥሩወርቅ የኮምፒውተር ጽሕፈት አገልግሎት በእሳቱ ሙሉ በሙሉ የወደሙ ሲሆን፣ ባለንብረቶቹ እንደሚሉት 1.3 ሚሊዮን ብር የሚገመት የንብረት ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡ ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት በተነሳው እሳት የእሳት አደጋ መከላከያ በወቅቱ ባለመድረሱና ዘግይቶ ከደረሰም በኋላ አቅሙ ውስን በመሆኑ፣ በንብረት ላይ የደረሰውን ጉዳት ማዳን እንዳልተቻለ የዓይን እማኞች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ እንደ እማኞቹ አስተያየት ያለምንም መከላከያ ለ20 ደቂቃዎች ያህል ሲቀጣጠል የነበረው እሳት፣ በመደብሮች ውስጥ የነበሩትን ጨርቃ ጨርቆችና ኮምፒውተሮች በፍጥነት ጋይተዋል፡፡ የእየሩሳሌም ጨርቃ ጨርቅ መደብር ባለቤት አቶ ጌቱ ደምቦባ ስለደረሰው ጉዳት ተጠይቀው፣ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ጣቃዎችና የተዘጋጁ ልብሶች ሙሉ በሙሉ መውደማቸውን ገልጸው፣ የእሳቱን መንስዔ በተመለከተ ለተጠየቁት ሲመልሱ፣ ማናቸውንም የኤሌክትሪክ ዕቃዎችንና ካውያዎችን በአግባቡ ካጠፉ በኋላ መደብራቸውን መዝጋታቸውንና እሳቱ ከየት እንደተነሳ እንደማያውቁ ለሪፖርተር ጠቁመዋል፡፡ የጥሩወርቅ ኮምፒውተር ጽሕፈት አገልግሎት ባለቤት በበኩላቸው፣ ከ300 ሺሕ ብር በላይ የሚገመቱ ኮምፒውተሮችና የፎቶ ኮፒ ማሽኖች እንዲሁም የስቴሽነሪ ቁሳቁሶች ሙሉ በሙሉ መውደማቸውን ገልጸዋል፡፡ በምሽቱ የተፈጠረውን እሳት ለመከላከል የሐዋሳ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ የእሳት አደጋ መከላከያና የከተማው የእሳት አደጋ መከላከያ በአጠቃላይ ሦስት ተሽከ

በሲዳማ ዞን ሁላ ወረዳ በግማሽ የበጀት አመት ቀጥታና ቀጥታ ካልሆኑ የገቢ አርዕስቶች ከ5 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ገቢ መሰብሰቡን የወረዳው ገቢዎች ባለስልጣን ንዑስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡

በሲዳማ ዞን ሁላ ወረዳ በግማሽ የበጀት አመት ቀጥታና ቀጥታ ካልሆኑ የገቢ አርዕስቶች ከ5 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ገቢ መሰብሰቡን የወረዳው ገቢዎች ባለስልጣን ንዑስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ከበደ መኩሪያ እንደገለፁት ገቢው ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከ1 ነጥብ 9 ሚሊዮን በላይ ብር ብልጫ እንዳለውና የእቅዱ አፈፃፀም 98 በመቶ መድረሱን ተናግረዋል፡፡ ለገቢው መገኘት ጉዳዩ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ክትትልና የቅርብ ድጋፍ ማድረጋቸው እንዲሁም ከማዘጋጃ ቤት ጋር በቅንጅት መስራቱ አስተዋጽኦ ማድረጉን አስረድተዋል፡፡በጽህፈት ቤቱ የገቢ አሰባሰብ የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ፍስሐ በኬ በበኩላቸው ለባለሙያዎች በገቢ አሰባሰብ ስርአት የሚሰጠው የግልፀኝነት፣ የተጠያቂነትና የስነ ምግባር ትምህርት ስራቸውን በታማኝነት እንዲሰሩ አድርጓቸዋል ማለታቸውን የዞኑ ባህል ቱሪዝምና የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ዘግቧል ፡፡ ፡፡

ሀዋሳ ውስጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሻቀበ የመጣውን የወላጅ አጥ ህፃናት ቁጥር ችግር ለመፍታታ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የከተማው ሴቶች ህፃናትና ወጣቶች መምሪያ አስታወቀ፡

Image
ሀዋሳ ውስጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሻቀበ የመጣውን የወላጅ አጥ ህፃናት ቁጥር ችግር ለመፍታታ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የከተማው ሴቶች ህፃናትና ወጣቶች መምሪያ አስታወቀ፡፡መምሪያው ከተለያዩ የዕምነት ተቋማትና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር በመተባበር በሀገሪቱ አዲስ የሆነውን የፎስተር ኬር ኘሮግራም እንደሚጀምርም ገልጿል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ ሴቶች ህፃናትና ወጣቶች መምሪያ በሀገሪቷ በቅርቡ ተግባራዊ መደረግ የተጀመረውን የፎስተር ኬር ኘሮግራም ለተለያዩ ባለድርሻ አካላት እያስተዋወቀ ይገኛል፡፡ከቢታኒ ቤተክርስትያን ሰርቪስና ከርሆቦት ዴቨሎኘመንት ኤንድ ሳፓርቲንግ ኦርጋናይዜሽን ጋር በመተባበር ለወንጌላዊያን አብያተክርስትያናት መሪዎች መምሪያው ባዘጋጀው የምክክር ስብሰባ ላይ እንደተባለውም በከተማው የፎስተር ኘሮግራም ለመጀመር ቅድመ ዝግጅቱ ተጠናቋል፡፡ የመምሪያው ኃላፊ ወይዘሪት ስምረት ግርማ እንዳሉት ከ4 ወራት በኋላ የሚጀመረው የፎስተር እንክብካቤ በከተማው በህፃናት ማሳደጊያ ተቋማት የሚገኙ ከ2ዐዐ በላይ ህፃናትን ጨምሮ በየደረጃው በጐዳና ላይ ያሉት ወደ ሁለት ሺህ የሚጠጉ ህፃናት ተጠቃሚ ይሆናሉ፡፡በኘሮግራሙ ወላጅ አጥ ህፃናትና ተጋላጭ የሆኑ ቤተሰቦች ድጋፍ ያገኛሉ ያሉት ወይዘሪት ስምረት ወላጅ አጥ ህፃናት የቤተሰብ ፍቅር አግኝተው እንዲያድጉ ከቤተሰቦቻቸው ካልሆነም ፈቃደኛ ከሆኑ ሌሎች ቤተሰቦች እንዲያድጉ እንደሚደረግ ገልፀዋል፡፡ ኘሮግራሙ የህፃናትን ችግር ለመፍታት ከሚደረጉ ዘርፈ ብዙ ተግባራት አንዱ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡ ህፃናቱን የሚያሳድጉ ቤተሰቦች በየእምነት ተቋሙ የሚመለመሉ በመሆናቸው የእምነት ተቋማት ሲወርድ ሲዋረድ የመጣውን የህዝቡ የመተሳሰብና የመተባበር ባህል በማጐልበትና በማሳመን ሞራላዊና መንፈሳዊ ግዴታቸው እንዲወጡም

በሲዳማ ዞን በሁሉም ቀበሌያት 2ዐ5 ሺህ 9 መቶ 24 ሄክታር መሬት በተፋሰስ ለማልማት ከታቀደው 75 በመቶ ማከናወን መቻሉን የዞኑ ግብርና ልማት መምሪያ ገለፀ፡፡

በሲዳማ ዞን ሁላ ወረዳ በግማሽ የበጀት አመት ቀጥታና ቀጥታ ካልሆኑ የገቢ አርዕስቶች ከ5 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ገቢ መሰብሰቡን የወረዳው ገቢዎች ባለስልጣን ንዑስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ከበደ መኩሪያ እንደገለፁት ገቢው ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከ1 ነጥብ 9 ሚሊዮን በላይ ብር ብልጫ እንዳለውና የእቅዱ አፈፃፀም 98 በመቶ መድረሱን ተናግረዋል፡፡ ለገቢው መገኘት ጉዳዩ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ክትትልና የቅርብ ድጋፍ ማድረጋቸው እንዲሁም ከማዘጋጃ ቤት ጋር በቅንጅት መስራቱ አስተዋጽኦ ማድረጉን አስረድተዋል፡፡በጽህፈት ቤቱ የገቢ አሰባሰብ የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ፍስሐ በኬ በበኩላቸው ለባለሙያዎች በገቢ አሰባሰብ ስርአት የሚሰጠው የግልፀኝነት፣ የተጠያቂነትና የስነ ምግባር ትምህርት ስራቸውን በታማኝነት እንዲሰሩ አድርጓቸዋል ማለታቸውን የዞኑ ባህል ቱሪዝምና የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ዘግቧል ፡፡ ፡