የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የተፋሰስ ልማትን ለማጠናከር በውሃ ሀብት ላይ ያተኮሩ ሶስት የምርምር ፕሮጀክቶችን እያካሄደ ነዉ
አዋሳ, መጋቢት 14 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በኢትዮጵያ የተጀመረውን የተፋሰስ ልማት ለማጠናከር በውሃ ሀብት ላይ ያተኮሩ ሶስት የምርምር ፕሮጀክቶችን እያካሄደ መሆኑን አስታወቀ ። አለም አቀፍ የውሃ ቀን " ውሀና ምግብ ዋስትና ለሁሉም " በሚል መሪ ቃል ከትናንት ጀምሮ ለሁለት ቀናት በዩኒቨርስቲው ዋናው ግቢ በፓናል ውይይትና በፎቶ ግራፍ አውደ ርእይ ተከብሯል፡፡ የዩኒቨርስቲው ምሁራን በፓናል ውይይቱ ላይ እንዳስረዱት በሀገራችን የተጀመረው የተፋሰስ ልማት ውሃን በአግባቡ ለመጠበቅና ለመጠቀም በተለይም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ያለዉ አስተዋጾኦ ከፍተኛ ነዉ ። በዩኒቨርስቲው የመስኖና ውሃ ሀብት ምህንድስና ትምህርት ክፍል ሃላፊ አቶ ሄኖክ ጥላሁን እንደገለጹት የተጀመሩትን አበረታች የተፋሰስ ልማት ስራዎች ይበልጥ ለማጠናከር የርምር ፕሮጀክቶቹ እየተካሄዱ ያሉት በደቡብ ክልል በሀዋሳ ሀይቅ ፣ በብላቴ ወንዝና ሌሎች የተፋሰስ አካባቢዎች ላይ ነዉ ። ከምርምሮቹም መካከል በሀዋሳ ሀይቅ ላይ ከከተማው የተለያዩ አቅጣጫዎች ከሚለቀቁ ዝቃጭ ቆሻሻዎች ለመታደግና የሃይቁን ደህንነቱ ለመጠበቅ ብሎም ለልማት እንዲውል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት እየሰሩና የአቅም ግንባታ ድጋፍ እያደረጉ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ በደቡብ ክልል ከሚገኙ መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የሚያካሄዳቸው የምርምር ስራዎች ወደሌሎችም የሀገራችን አካባቢዎች በማስፋፋት የድርሻውን እንደሚወጣ ተናግረዋል፡፡ የዩኒቨርስቲው የባዮ ሲስተምና ኢንቫይሮሜንታል ምህንድስና ዲፓርተመንት መምህር አቶ አሰግድ ቸርነት በበኩላቸው በተለይ ተማሪዎችንና ወጣቶች የውሃን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ በውል ተገንዝበው እን