በሐዋሳ ከተማ ህገወጥ ነጋዴዎችና ፖሊሶች ሲታኮሱ አደሩ
የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ክልል ዋና ከተማ በሆነችው ሐዋሳ፣ ባለፈው ረቡዕ ምሸት ፖሊሶችና የኮንትሮባንድ ነጋዴዎች ሲታኮሱ አደሩ፡፡ በተደረገው የተኩስ ልውውጥ የደረሰውን የጉዳት መጠን ለማወቅ ባይቻልም አንድ ህፃን መቁሰሉን የክልሉ ፖሊስ አስታውቋል፡፡በከተማው ሐይቅ ዳር ክፍለ ከተማ ውስጥ በሚገኘውና በተለምዶ ገበያ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ፣ ባለፈው ረቡዕ ከምሽቱ 4፡30 ላይ የተጀመረው የተኩስ ልውውጥ እስከ ሌሊቱ ስምንት ሰዓት ድረስ ቀጥሎ መቆየቱንና በዚህ ምክንያትም የተመቱና የቆሰሉ ሰዎች በአዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል ሕክምና ሲደረግላቸው እንደቆዩ ምንጮች ለአዲስ አድማስ አስታውቀዋል፡፡ የተኩስ ልውውጡ መንስኤ ከኮንትሮባንድ ንግድ ጋር የተገናኘ መሆኑን የገለፁልን የክልሉ የወንጀል መከላከል ዋና የሥራ ሂደት ባለቤት ኮማንደር በላይነህ በላይ፤ በህገወጥ መንገድ የገቡና የተከማቹ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች እንዳሉ ለፖሊስ ጥቆማ ደርሶት ወደ ስፍራው እንደሄዱ ተናግረዋል፡፡ ቦታው ሲደርሱ ኮንትሮባንድ ነጋዴዎቹ ያደራጇቸውና ኮንትሮባንድ ዕቀዎቹን በመጫን፣ በማውረድና በመበለት ሥራ ላይ የተሰማሩ ወጣቶች በጉምሩክ ሠራተኞችና በፀጥታ ኃይሎች ላይ ጉዳት ለማድረስ መሞከራቸውን ኮማንደር በላይነህ ገልፀዋል፡፡ በህገወጥ ነጋዴዎቹ የተደራጁት ወጣቶች፣ መሣሪያ ታጥቀው ነበር ያሉት ኮማንደሩ፤ በፀጥታ ኃይሎቹና በጉምሩከ ሠራተኞቹ ላይ ድንጋይ በመወርወር ጉዳት ለማድረስ ከመሞከራቸውም በላይ ኦፕሬሽኑን ሠላማዊ በሆነ መንገድ ለማከናወን በሄደው የፌደራል፣ የክልሉና የከተማው የፀጥታ ኃይሎችና በጉምሩክ ሠራተኞች ላይ ተኩስ መክፈታቸውን ጠቁመው፤ በተኩስ ልውውጡ ከየትኛው ወገን እንደተተኮሰ ባልታወቀበት ሁኔታ አንድ ህፃን መቁሰሉን ገልፀዋል፡፡ ከችግሩ ጋር በተያያዘ 40 የሚደርሱ ሰዎች በቁ