የደቡብ ክልል ፕሬዚዳንት “እኔ ከተከሰስኩ ወ/ሮ አዜብ መስፍንም መከሰስ አለባቸው” አሉ (በመምህሩ መልካሙ)
New የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽፈራው ሽጉጤ በከፍተኛ የሙስና ወንጀል እንዲጠየቁ የክልሉ ፓርቲ ባደረገው ድርጅታዊ ግምገማ ውሳኔ አስተላለፈ። ፕሬዚዳንቱ “እኔ ብቻዬን መከሰስ የለብኝም። ከተከሰስኩም ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ባለቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ጋር መሆን አለበት” በማለት ስብሰባ ረግጠው መውጣታቸውን ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁ ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ ምንጮች አስታወቁ። አቶ መለስ ድርጅቱ የወሰነውን ውሳኔ ቀለበሱ። በዚህም ሳቢያ በደቡብ ክልል የውስጥ ለውስጥ ሽኩቻና የፖለቲካው ውጥረት ተባብሶ ቀጥሏል፡፡ ይህ የሆነው ከየካቲት 5 ቀን እስከ የካቲት 11 ቀን 2004 ዓም ድረስ የደቡብ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥትን የሚመራው የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ደኢህዴን) የከፍተኛ አመራር ግምገማ ባካሄደበት ወቅት ነው። የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) የመረጃ ምንጮች እንደገለጹት በክልሉ በተካሄደው ከባድ የተባለ ግምገማ ቅድሚያውን የያዙት የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ነበሩ። የሲዳማ ቡና ላኪዎች ማህበር አባልና በማህበሩ ከፍተኛ ባለአክሲዮን እንደሆኑ በግምገማ የቀረበባቸው ፕሬዚዳንቱ፣ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ መዝብረዋል በሚል ጠንካራ አውጫጪኝ ተካሄዶባቸዋል። በኢህአዴግ የፖለቲካ ቋንቋ አቶ ሽፈራው ሽጉጤን በ”ኪራይ ሰብሳቢነትና በሙሰኝነት” ተፈርጀዋል። እንደ መረጃ ምንጮቹ ገለጻ ፕሬዚዳንቱ ከሥልጣን ወርደው በህግ እንዲጠየቁ ድርጅታዊ ውሳኔ ሲበየንባቸው፣ ”እኔ ብቻዬን አይደለሁም፣ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ባለቤት ወይዘሮ አዜብ መስፍን ጋር በጋራ ገንዘቡን ወስደናል፡፡ የምንጠየቅም ከሆነ ሁለታችንም በህግ ፊት መቅረብ አለብን፡፡ ብሩን መመለስም ካለብን ሁለታችንም እንመልስ” በማለት የግምገማ መድረ