Posts

Old Sidama Song Stuff

Image

የሀዋሳ ሀይቅን ከብክለትና ከደለል የመከላከል ሥራ በማህበር በተደራጁ ወጣቶች እየተከናወነ ነው

Image
ሀዋሳ ፤የካቲት 03 2004 /ዋኢማ/ -  በሀዋሳ ከተማ በማህበራት የተደራጁ ወጣቶች የሀዋሳ ሀይቅን ከብክለትና ከደለል የመከላከል ሥራዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኙ የከተማው ማዘጋጃ ቤት አስታወቀ፡፡ በማዘጋጃ ቤቱ የአካባቢ ጥበቃ መምሪያ ሃላፊ አቶ ተፈራ ባንቶ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንዳስታወቁት የሀዋሳ ሀይቅን ከብክለትና ከደለል የመከላከል ሥራዎችን በማከናወን ላይ የሚገኙት በ20 የአካባቢ ጥበቃና ጽዳት ማህበራት የተደራጁ 378 ወጣቶች ናቸው ፡፡ ወጣቶቹ በሀይቁ ዙሪያ የሚገኙ ደላሎችን ለመከላከል በሐይቁ የተፋሰስ መሬቶች ዙሪያ 16 ኪሎ ሜትር የጎርፍ መቀልበሻ ቦዮችን እና የዝናብ ውሃን ወደ መሬት ለማስረግ የሚያስችሉ 57 የጨረቃ እርከኖችን መገንባታቸውን ሃላፊው አስረድተዋል፡፡ እንዲሁም የአካባቢውን ሥነ ምህዳር ከመጠበቅ በተጨማሪ ለውበት ለጥላና ለመናፈሻ አገልግሎት ሊውሉ የሚችሉ ከ92 ሺህ በላይ የአገር በቀል እና የባህር ማዶ ችግኞችን መትከላቸውን አመልክተዋል፡፡ በማህበር ተደራጅተው በእንቅስቃሴ ላይ የሚገኙት ወጣቶች ቀደም ሲል ሥራ አጥ እና በተለያዩ ሱሶች የተጠመዱ እንደነበሩ ያስታወሱት ሃላፊው በአሁኑ ወቅት ግን ለራሳቸው ከፈጠሩት የሥራ ዕድል በተጨማሪ ለሀዋሳ ሐይቅ እና ለከተማው አካባቢ ጥበቃ ሥራ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከቱ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡ የከተማው ማዘጋጃ ቤትም ወጣቶቹ እያከናወኑ የሚገኙት ሥራ አርአያነት ያለው ተግባር መሆኑን ከገመገመ በኋላ በየወሩ ለማህበራቱ አባላት የደሞዝ ክፍያ የሚውል የ150 ሺህ ብር ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ከሃላፊው ገለጻ ለመረዳት ተችሏል፡፡ http://www.waltainfo.com/index.php?option=com_content&view=article&id=175

ሐዋሳ ዩኒቨርስቲ የማኀበረሰብ ተኮር ሬዲዮ ጣቢያ ለመክፈት የሚያስችል ፈቃድ አገኘ

Image
አዲስ አበባ, የካቲት 3 ቀን 2004 (አዲስ አበባ) - ሐዋሳ ዩኒቨርስቲ የማኀበረሰብ ተኮር ሬዲዮ ጣቢያ ለመክፈት የሚያስችለውን ፈቃድ ወሰደ፡፡ የዩኒቨርሲቲው የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ማርኬቲንግ ዳይሬክተር የሕዝብ ግንኙነት ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ዳዊት በዳሳ ለኢ ዜ አ እንዳስታወቁት ዩኒቨርሲቲው ፈቃዱን ያገኘው ባቀረባቸው ምክረ ሃሳብ /ፕሮፖዛል/ ከሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ተወዳድሮ በማሸነፉ ነው፡፡ በፈቃዱ ከኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን አስፈላጊ መስፈርት መሟላታቸው ከተረጋገጠ በኋላ ዩኒቨርሲቲው በኤፍ ኤም 90 ነ ጥብ 9 የአየር ሞገድ ፕሮግራሞችን ማቅረብ ይጀምራል ብለዋል፡፡ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ዮሴፍ ማሞ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው ባሉት አራት ካምፓሶች በአሁኑ ወቅት ከ24 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በመደበኛና በተከታታይ ፕሮግራሞች እስከ ዶክትሬት ዲግሪ ባሉት ደረጃዎች እያስተማረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ እንዲሁም በይርጋለም ከተማ ላይ ግንባታው በመፋጠን ላይ በሚገኘው ካምፓስ ከመጪው ዓመት ጀምሮ ተማሪዎችን እንደሚቀበል ገልጸዋል፡፡ በአሁኑ ወቅትም 120 የሚሆኑ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ችግር ፈቺና አሳታፊ የምርምር ሥራዎች በዩኒቨርስቲው ሥር በመካሄድ ላይ የሚገኙ ሲሆን የሬዲዮ ጣቢያው መከፈት ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል፡፡ በመሆኑም የዩኒቨርሲቲው የማኀበረሰብ አገልግሎት ከማጠናከር በተጨማሪ፤ የቴክኖሎጂ ሽግግር ለመፍጠር የሚደረገውን ጥረት ለማጠናከር ሬዲዮውን በዋናነት ለመጠቀም መዘጋጀቱን አስታውቀዋል፡፡ ሬዲዮ ጣቢያውን ለመክፈት የሚያስችለውን ወጪ በኢትዮጵያ የአሜሪካን ኤምባሲ የተሸፈነ ሲሆን፣ ከአንድ ወር በኋላ ለሐዋሳ ከተማና አካባቢው ማኀበረሰብ ሥርጭት እንደሚጀምር መግለጻቸውን

Ethiopia gears up for African coffee conference, exhibition

Image
The Eastern African Fine Coffees Association (EAFCA) will hold the 9th edition of the African Fine Coffee Conference and Exhibition in Ethiopia next week. The  event will be held in Addis Ababa from February 16 to 18. Organisers said it will provide delegates an opportunity to experience Ethiopia's vast coffee varieties and those from other coffee producing countries. The event is expected to play a significant role in building a positive image for Ethiopia, as well as promoting knowledge transfer and creating market connections, according to Abdullah Bagersh, EAFCA's general manager for the Ethiopian chapter. The conference aims to raise issues of sustainable production systems, climate change, market outlook, growing potential of Robusta and to learn from the Ethiopian experience amongst others. "The exhibition will also serve as a significant platform for highlighting the best coffees in Ethiopia," Bagersh said. "It is also expected that the ev

Invest in Sidama

Image
Sidama zone covers 6972.1 square kilometer And lies between 6.14-7.18 latitude and 37.92to 39.19 longitudes, with an elevation ranging 501-3000 meters above see level. The zone is divided in 19 Woredas with a total population of 3019442 (2007). Regarding the Agro – Ecology of the zone, out of the total land size 26.8% is kolla, 45.49% Weinadega and 27.71% Dega. The annual mean temperature of the zone ranges between 10.1-27o c and the annual mean rainfall ranges 801- 1600 mm. According to the land utilization data of the region, 50.67% is cultivated land, 17.57% grazing land, 6.51% forest bushes and shrub land, 17.84 % cultivable, and the remaining 7.41% is covered by others. Sidama zone has a total length of 1173.8 km. all weather road , of the total length 96.5 km. is tarmac road 857 km graveled and 52 km is partially graveled. Sidama zone ranks first in the region, by coffee production. Annually, more than twenty thousand tones of cleaned coffee is sent to the central mark