Posts

ቢ ጂ አይ ቢራ ፋብሪካ በ12 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነባው የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ መሣሪያ አገልግሎት መስጠት ጀመረ

አዋሳ, ህዳር 28 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - በሀዋሳ ከተማ የሚገኘው ቢ ጂ አይ ቢራ ፋብሪካ በ12 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነባው የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ መሣሪያ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አስታወቀ፡፡ የፋብሪካው ኮርፖሬት ተቆጣጣሪ አቶ በቀለ ሰሙ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ተከላው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረው መሣሪያ ፋብሪካው ለቢራ ጠመቃ አገልግሎትና ለጠርሙሰ አጠባ የሚጠቀምበትን ፍሳሽ ከኬሚካል ነጻ በማድረግ በአካባቢ ላይ የሚደርሰውን ብክለት ለመከላከል ያስችላል፡፡ በመሳሪያው አማካይነት ተጣርቶ የሚወጣውን ውሃ በአካባቢው የሚገኙ ነዋሪዎች ለመስኖ አገልግሎት መጠቀም እንደሚችሉ ተናግረዋል። ፋብሪካው የተለያዩ ማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማትን በመገንባት በአካባቢው የሚገኙ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በአንድ ቢሊዮን ብር ካፒታል ተገንብቶ ባለፈው ግንቦት ወር የሙከራ ስራ የጀመረው ቢ ጂ አይ ቢራ ፋብሪካ በአሁኑ ወቅት በቀን 363 ሺህ 600 ጠርሙስ ቢራ በማምረት ላይ የሚገኝ መሆኑን ገልፀው ለ273 ሰዎች የስራ እድል መፍጠሩንም አስታውቀዋል፡፡ ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ ማምረት ሲጀምርም የማምረት አቅሙ በእጥፍ እንደሚጨምር አቶ በቀለ ተናግረዋል፡፡ የደቡብ ክልል ንግድ ኢንደስትሪና ከተማ ልማት ቢሮ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች የስራ ሂደት ባለቤት አቶ አበበ ደንጋሞ በበኩላቸው የፍሳሽ ቆሻሻ በአካባቢ ላይ የሚያደርሰውን ብክለት ለመከላከል ፋብሪካው ያከናወነው ተግባር ለሌሎች ፋብሪካዎች አርአያ ሊሆን እንደሚችል አስታውቀዋል፡፡

Kabu Coffee, to Provide Export Standard Ethiopian Coffee

Kabu Coffee has announced plans to market export standard Ethiopian coffee. The company has expanded its investment capital to 10 million birr for this venture. Kabu is marketing high quality roasted coffee to international and domestic customers according to Aman Adinew company advisor. The company aimed to venture out in this direction from the outset he said. Kabu strives to carefully control the quality of its ingredients to ensure the quality service promised by its slogan ‘Coffee Redefined’ said Aman. Adding value to Ethiopia’s number one export, coffee, is sure to make the sector more profitable explains Aman. Ethiopia needs to become competitive in the international roasted coffee market dominated by Europeans he said.  Kabu is partnering with a German firm to introduce roasted and instant coffee into the national market. The company believes that coffee roasted and prepared from Ethiopia and not blended with other types of Coffee will be warmly welcomed on the interna

Debub Global to Enter Ethiopian Banking Sector

Debub Global Bank Share Company is to enter the Ethiopian banking sector in 2012. The Bank has raised 286 million birr in subscribed capital and 150 million in paid up capital through the sale of shares. 5481 shares have been presented to the National Bank pending signature and verification by shareholders according to an official at the Bank. Debub Global Bank expects to concentrate its activities in the South of Ethiopia where there exists untapped potential for investment said the official. The shareholders of the bank understand the potentials in the South and are interested in engaging in investment and trade in the area explained the official. The General Assembly of the bank has presented a list of people who could potentially serve on its board of directors and has waited six months, after meeting all requirements, to begin operations explained the official. The National Bank reviewed the thirty potential nominees to the board of directors according to their credentials

በሲዳማ ዞን ከ113 ሚሊዮን ብር የሚበልጥ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሀብቶች ፈቃድ ተሰጠ

አዋሳ, ህዳር 26 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - በሲዳማ ዞን በበጀት አመቱ የመጀመሪያው ሩብ አመት ከ113 ሚሊዮን ብር የሚበልጥ ካፒታል ላስመዘገቡ 25 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን የዞኑ ንግድና ኢንደስትሪ መምሪያ ገለጸ። በመምሪያው የኢንቨስትመንት የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ብርሃኑ ወልደሚካኤል ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ባለሀብቶቹ የሚሰማሩባቸው የስራ መስኮች በግብርና፣ በኢንዱስትሪና ማህበራዊ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ለመሰማራት ነው። በሩብ ዓመቱ ፈቃድ የወሰዱት ባለሀብቶች ቁጥር ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት በሁለት ባስመዘገቡት ካፒታል በ30 ሚሊዮን ብር ብልጫ እንደነበረው ገልጸው ባለሀብቶቹ 3 ሺህ ሄክታር መሬት በማግኘታቸው ሙሉ ለሙሉ ወደ ስራ ሲገቡ ከ4 ሺህ 500 ለሚበልጡ ሰዎች የስራ እድል እንደሚፈጥሩ ተናግረዋል። መምሪያው ለባለሀብቶቹ አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸው የተሰጣቸው ያላለሙና ለሌላ ሶስተኛ ወገን አሳልፈው የሰጡ 19 ባለሀብቶች የወሰዱትን ቦታ በመመለስ ፈቃዳችው እንዲሰረዝ ማድረጉን ጠቁመዋል። በዞኑ ወርቅ ታንታለምና የማእድን ውሃና ለተለያየ አገልግሎት የሚውል ሰፊ መሬት እንደሚገኝ ጠቁመው በመስኩ መሰማራት ለሚፈልጉ ባለሀብቶች መምሪያው አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

በሲዳማ ዞን በወንሾ ወረዳ የተሻሻለ የቡና ዝርያ በመሰራጨት ላይ ነው

አዋሳ, ህዳር 26 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - በሲዳማ ዞን በወንሾ ወረዳ ለሚገኙ አርሶ አደሮች በሽታና ድርቅን መቋቋም የሚችሉና የተሻለ ምርት የሚሰጡ የቡና ዝርያዎች በመሰራጨት ላይ መሆኑን የወረዳው ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለጸ። የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ በቀለ ሁሞ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በወንዶ ገነት ደን ኮሌጅና በጅማ ግብርና ምርምር ተቋም በአዋዳ ማዕከል በምርምር የተገኙ ከፍተኛ ምርት የሚሰጡና በሽታና ድርቅ መቋቋም የሚችሉ ከግማሽ ሚሊዮን የሚበልጥ ሶስት ዓይነት የሲዳማ ስፔሻሊቲ ቡና ዝርያዎች እየተሰራጩ ነው። በመሰራጨት ላይ የሚገኙት የቡና ዝርያዎች በሁለት አመት ጊዜ ምርት መስጠት የሚችሉና ከነባሩ የቡና ዝርያ ጋር ሲነጻጸር ከ8 እስከ 12 ኩንታል ብልጫ ያለው ምርት በሄክታር መስጨት የሚችል መሆኑን ተናግረዋል። አዲስ በመሰራጨት ላይ የሚገኘው የቡና ዝርያ እስካሁን ከስድስት መቶ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች መሰራጨቱንና በሄክታር ከ20 እስከ 25 ኩንታል ምርት መስጠት እንደቻለ አቶ በቀለ ገልጸዋል። በመጪው ሚያዚያ 2004 ለአርሶ አደሮች የሚሰራጭ ከስድስት መቶ ሺህ በላይ የሲዳማ ስፔሻሊቲ ቡና ችግኝ በመዘጋጀት ላይ መሆኑን ጠቁመው በመንግስት ችግኝ ጣቢያ ብቻ የሚዘጋጀው የቡና ችግኝ በቂ ባለመሆኑ በሞዴል አርሶ አደሮች ማሳ እንዲባዛ እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል። የቡና ችግኙን በማልማት ላይ ከሚገኙት አርሶ አደሮች መካከል አርሶ አደር አፀደ ጎኔሶ እንደገለጹት በምርምር ከተገኘው የቡና ዝርያ ለሙከራ ወስደው ካለሙት 700 ችግኝ ያገኙት ምርት ከፍተኛ በመሆኑ ችግኙን በብዛት ወስደው ለማልማት ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል።