Posts

በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች አዳማ፤ አዲስ አበባና ሐዋሳ የተሻሉ ተሞክሮዎች ያላቸው ናቸው ተባለ

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 21፣ 2004 (ኤፍ ቢ ሲ) በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች አዳማ፤ አዲስ አበባና ሐዋሳ የተሻሉ ተሞክሮዎች ያላቸው ናቸው ተባለ። ሶስተኛው  የከተሞች ቀንን ምክንያት በማድረግ በመቀሌ ከተማ እየተካሄደ ያለው ዝግጅት ዛሬም ቀጥሎ ውሏል። የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን በተመለከተ አየተካሄደ ባለው  የፓናል ወይይት ላይ የኤጀንሲው  ዳይሬክተር አቶ ገብረ መስቀል ጫላ እንደተናገሩት ከተሞች የተሻሉ እንዲሆኑ ያስቻላቸው  የቴክኒክና ትምህርት ሙያና የብድር ተቋማት ጋር በጥምርት በመስራታቸው ነው። ሌሎች የሀገሪቱ ከተሞችም ከእነዚህ በየከተሞቻቸው ከተደራጁት የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልምድ  ሊወስዱ ይገባል blewal.

የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የጋዜጠኝነትና ኮሚኒኬሽን የትምህርት ፕሮግራም ከፈተ፤ በአምስት የትምህርት መስኮችም የድህረ ምረቃ ኘሮግራም ሊጀምር ነው

ሃዋሳ, ህዳር 21 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በተያዘው የትምህርት ዘመን የጋዜጠኝነትና ኮሚኒኬሽን የትምህርት ፕሮግራም በመጀመሪያ ዲግሪ መክፈቱን አስታወቀ፡፡ በአምስት የትምህርት መስኮችም የድህረ ምረቃ ኘሮግራም ሊጀምር ነው፡፡ የዩኒቨርሰቲው የማህበረሰብና ሂዩማኒቲ ኮሌጅ ዲን ዶክተር ንጉሴ መሸሻ ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንዳስታወቁት ዩኒቨርስቲው ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ በጋዜጠኝነትና ኮሚኒኬሽን የትምህርት ፕሮግራም ከ30 በላይ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ጀምሯል፡፡ ፕሮግራሙ የተከፈተው ለመማር ማስተማሩ ስራ የሚያስፈልጉ ዝግጅቶች ከተሟሉ በኋላ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በተለይ ተማሪዎች ከንድፈ ሀሳብ ትምህርት በተጨማሪ በተግባር የተደገፈ ልምምድ የሚያደርጉበት በዩኒቨርስቲው የማህበረሰብ ሬዲዮ እንዲሁም ከደቡብ ክልል መንግስት ጋር በመተባበር የክልሉን ኤፍ ኤም ሬዲዮና ቴሌቭዥን ለመጠቀም ምቹ ሁኔታ በመፈጠር ላይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የፕሮግራሙ መከፈት ብቃት ያለው የመገናኛና የኮሚኒኬሽን ባለሙያ በጥራት በማፍራት ሀገሪቱ ለተያያዘችው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ስኬታማነት አስተዋጾኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል፡፡ ከዚህም ሌላ ዩኒቨርስቲው በጋዜጠኝነትና ኮሚኒኬሽን ፣ እንግሊዘኛን እንደ መነጋገሪያ ቋንቋ ማስተማር ፣ የባህልና ዘርፈ ብዙ የቋንቋዎች ጥናት፣ ሶሻል አንትሮፖሎጂ ፣ ማስታወቂያና ህዝብ ግንኙነት የትምህርት መስኮች የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች ለመጀመር ዝግጅት እያደረገ መሆኑንም አመልክተዋል፡፡ ለዚሁ ኘሮግራም የስርዓተ ትምህርት ቀረጻና ግምገማ፣ የመምህራን ምደባና የመሳሰሉ ዝግጅቶች በማካሄድ ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡ በእያንዳንዱ ፕሮግራምም ከ10 በላይ ተማሪዎችን ተቀብለው እንደሚያሰ

Mugher & Hawassa kick off new EPL season with victories

Image
Mugher Cement FC Addis Ababa, Ethiopia  – Defending champions Ethiopian Coffee were held to a 2-2 draw by the visiting Harar Brewery as the 2011/12 Ethiopia Premier League season kicked off here today. Mugher Cement collected three points with a 2-1 victory in Dire Dawa, while Hawassa City scored narrow win (1-0) at home against the newly promoted Ethiopian Air Force team. The league will continue here tomorrow with two EEPCO vs Sidama Coffee and CBE taking on Adama City. The matches featuring St. George vs Defence Force and Dedebit FC vs Arba Minch City, another newly promoted team, were postponed as they had a number of players selected for the Ethiopian Walia national team, which is currently in Dar es Salaam for the CECAFA Senior Challenge Cup. After one game, Mugher Cement and Hawassa City are in the lead with 3 points and +1 goal. Week 1 Results: Sunday: November 27, 2011 Addis Ababa : Ethiopian Coffee vs Harar Brewery 2-2 Dire Dawa:  Dire Dawa City vs Mug

Ethiopia Premier League: EEPCO 1 Sidama Coffee 0, CBE 1 Adama 1

Image
Published By  Markos Berhanu  On Monday, November 28th 2011. Under  Ethiopian Soccer    Tags:   Addis Ababa , Commercial Bank of Ethiopia ,  EEPCO ,  Ethiopia Premier League    Addis Ababa –  EEPCO kicked off their 2011/12 Ethiopia Premier League season with a 1-0 victory over last year’s Cinderella team, Sidama Coffee. The day’s other double header featuring Commercial Bank of Ethiopia (CBE) and Adama City, ended in a 1-1 draw. The league officially kicked off here yesterday when defending champions Ethiopian Coffee were held to a 2-2 draw by Harar Brewery. The visitors led 1-0 at half-time thanks to a goal by Amha Belete, and it wasn’t until 15 minutes before regulation time that the defending champions equalized through Dawit Estifanos. However, Coffee’s euphoria didn’t last long as Amha Belete hits his second goal two minutes later. The Harari team decided to play a more defensive style to maintain their lead, but Medhane Tadesse scored the equalizer in injury time

የኤርትራን መንግስት አስከፊ ስርዓት ለማስወገድ የሚያስችል አዲስ የስትራቴጂ ትግል የሚቀይስ የኤርትራ ብሄራዊ ጉባዔ ለዴሞክራሲያዊ ለውጥ ውይይት በሐዋሳ ተጀምሯል፡፡

Image
የኤርትራ ኮሚሽን ለዴሞክራሲያዊ ለውጥ የኤርትራ ተቃዋሚ ኃይሎች ልዩነታቸውን አጥብበው የሀገሪቱን አምባገነን ስርዓት እንዲያስወግዱ ጥሪ አቀረበ ማክስኞ, 22 ህዳር 2011 16:23 የኤርትራ ህዝብ የጭቆና አገዛዝን በመቃወም ለበርካታ ዓመታት የታገለ ቢሆንም ከነጻነትም በኋላ በአምባገነን ስርዓት ለመገዛት ተገዷል፡፡ በውጤቱም የኤርትራ መንግስት በሚከተለው የአፈናና አገዛዝ ሀገሪቱ የሰብአዊ መብት የሚረገጥባትና ዜጎች በአፈና እና በፍርሃት የሚኖሩባት ለመሆን በቅታለች፡፡ በመሆኑም የኤርትራን መንግስት አስከፊ ስርዓት ለማስወገድ የሚያስችል አዲስ የስትራቴጂ ትግል የሚቀይስ የኤርትራ ብሄራዊ ጉባዔ ለዴሞክራሲያዊ ለውጥ ውይይት በሐዋሳ ተጀምሯል፡፡ ጉባዔው ከዚህ በፊት የተቋቋመው የኤርትራ ኮሚሽን ለዴሞክራሲያዊ ለውጥ ባለፉት 16 ወራት የደረሰበትን አፈጻፀም ይገመግማል፡፡ የኤርትራ ኮሚሽን ለዴሞክራሲያዊ ለውጥ ሊቀመንበር አምሃ ዶሞኒካ ፍትህና ዴሞክራሲ የናፈቀውን የኤርትራን ህዝብ ከአምባገነን ስርዓት የማላቀቅ ጊዜው አሁን ነው ብለዋል፡፡ በመሆኑም የስርዓቱ በርካታ ተቃዋሚዎች ልዩነታቸውን በማጥበብ የኤርትራን ህዝብ እንዲታደጉት ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብና መንግስትን አቋም ያቀረቡት የኢህአዴግ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሬድዋን ሁሴን በኤርትራ ህዝብ ጫንቃ ላይ የተጫነውን አምባገነን አገዛዝ ለማስወገድ የተለያዩ የኤርትራ ተቃዋሚ ኃይሎች አመርቂ ውጤት ማግኘት አልቻሉም፡፡ በመሆኑም የተጀመረው ጉባዔ የነበሩትን ችግሮች በማስወገድ የጋራ ግንዛቤና መግባባት ላይ እንደሚደርስ ያላቸውን እምነት ገልፀዋል፡፡ በኤርትራ ሰላምና ዴሞክራሲ ለማስፈን ለሚደረገው ትግልም ወንድም የሆነው የኢትዮጵያ ህዝብና መንግስትም አስፈላጊው ድጋፍ