Posts

በደቡብ ክልል መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ከሶስት ቢሊዮን በሚበልጥ በጀት የልማት ስራ እያካሄዱ ነው

አዋሳ, ህዳር 5 ቀን 2004 (ሃዋሳ) - በደቡብ ክልል መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በመደቡት ከሶስት ቢሊዮን ብር የሚበልጥ በጀት ህብረተሱቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ስራዎች በመካሄድ ላይ መሆናቸውን የክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ገለጸ፡፡ አብዛኛዎቹ ድርጅቶች የሚንቀሳቀሱት በሀዋሳ ከተማ ፣በሲዳማ ፣ በወላይታ ፣ በጋምጎፋ ፣ በሀዲያና በጉራጌ ዞኖች መሆኑን አስታውቀው የልማት ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ ሁሉንም የክልሉ ህዝብ በቀጥታና በተዘዋዋሪ ተጠቃሚ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል። የቢሮው ምክትል ሃላፊ አቶ ታፈሰ ገዳዎ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር እስከ 2015 የሚካሄዱት የልማት ስራዎች 490 ፕሮጀክቶች ናቸው፡፡ ፕሮጀክቶቹ በ202 መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እንደሚካሄዱ አመልክተው የልማት ስራዎቹ የሚያተኩሩት በግብርና ፣በጤና ፣በትምህርት ፣ በመጠጥ ውሃ ፣በመስኖና ሌሎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ባላቸው ዘርፎች መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አብዛኛዎቹ ድርጅቶች የሚንቀሳቀሱት በሀዋሳ ከተማ ፣በሲዳማ ፣ በወላይታ ፣ በጋምጎፋ ፣ በሀዲያና በጉራጌ ዞኖች መሆኑን አስታውቀው የልማት ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ ሁሉንም የክልሉ ህዝብ በቀጥታና በተዘዋዋሪ ተጠቃሚ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል። አፈጻጸማቸውን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ክትትልና ቁጥጥር እንደሚካሄድ ገልጸው መንግስታዊ ያልሆኑት ድርጅቶች ለመንግስት የልማት አጋር በመሆን የአምስት አመቱን የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድን ለማሰካት የበኩላቸው አስተዋጾኦ እንዳላቸ ገልጸዋል፡፡

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከሰማንያ የሚበልጡ የምርምርና ስርፀት ተግባራትን እያካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ህዳር 2 (ኤፍ ቢ ሲ) የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከሰማንያ የሚበልጡ የምርምርና  ስርፀት ተግባራትን እያካሄደ ነው። ዩኒቨርሲቲው እያካሄዳቸው ያሉ የምርምርና ስርፀት ስራዎች የአካባቢውን ህብረተሰብ  ችግሮች ሊፈቱ የሚችሉ ናቸው። ግብርና፣ ትምህርትና ጤና በምርምርና ስርፀቱ ትኩረት ተሰጥቷቸው  እየተሰሩ ያሉ መሆናቸውን የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ስርፀት ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶክተር ተስፋዬ አበበ ተናግረዋል።

የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ኤፍ ኤም ሬዲዮ ስርጭት ለመጀመር የሚስችል ዝግጅት እያደረገ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 28 (ኤፍ ቢ ሲ) የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ኤፍ ኤም ሬዲዮ ስርጭት ለመጀመር የሚስችል ዝግጅት እያደረገ ነው። በሬዲዮ ጣቢያው አስፈላጊነት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ትናንት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ የጋራ ውይይት ተካሂዷል፡፡ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ዮሴፍ ማሞ በዚሁ ወቅት እንዳሉት  የማህበረሰብ ኤፍ ኤም  ሬዲዮ ጣቢያው ስርጭት ዓላማ የተቋሙን የመማር ማስተማር፣ የምርምርና የህብረተሰብ አገልገሎት ለአካባቢው ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ነው፡፡ ጣቢያው ለጊዜው በ50 ኪሎ ሜትር ዙሪያ አገልግሎቱን የሚጀመር ሲሆን ቀስ በቀስም  የስርጭት አድማሱን እንደሚያስፋፋ ጠቁመዋል። 

የሃዋሳ ዩንቨርሲቲ ግማሽ ቢሊየን ብር በሚሆን ወጭ አዲስ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሊያስገነባ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26 (ኤፍ ቢ ሲ) የሃዋሳ ዩንቨርሲቲ ግማሽ ቢሊየን ብር በሚሆን ወጭ አዲስ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሊያስገነባ ነው። በአሁኑ ወቅት  የኢንስቲትዩቱን  ግንባታ ለማስጀመር የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት የተጠናቀቀ  ሲሆን ስራውም በአንድ  ወር ውስጥ  ይጀመራል  ተብሏል። ግንባታው የተማሪዎች  ማደሪያና የመማሪያ ክፍሎችን  ጨምሮ  ለተለያዩ  አገልግሎቶች የሚውሉ  ህንፃዎችን ያካተተ ነው። በሁለት ዓመት ጊዜ  ውስጥ  የኢንስቲትዩቱ ግንባታ  ሲጠናቀቅ  17 ሺ የነበረውን የዩኒቨርሲቲውን  የተማሪዎች ቅበላ አቅም ወደ 30 ሺ ከፍ እንደሚል በዩንቨርሲቲው የግንባታ ዘርፍ ዳይሬክተር አቶ ደንበሹ ኔኤሬ ለኤፍ ቢ ሲ  ተናግረዋል። እንደ ባልደረባችን ጥላሁን ካሳ ዘገባ የሃዋሳ ዩንቨርሲቲ ባለፉት 3 አመታት በ480 ሚሊየን ብር ሲያካሂድ የነበረውን የማስፋፊያ ግንባታ ሙሉ በሙሉ አጠናቋል።

South to supply 171,000 tons coffee to central market

South, October 23, 2011 (Hawassa) - Some 171,000 tons coffee will be supplied to the central market from South Ethiopia Peoples' State in the current Ethiopian budget year, the regional marketing and cooperatives bureau said. Speaking at a day long relevant workshop in Hawassa Town of the state on Saturday Deputy bureau head, Abraham Demissie said the amount will exceed by more than double that of same time in the previous budget year. More than 75,440 tons coffee was supplied to market during the last budget year. Abraham said a total of 290,000 tons of coffee is expected to be harvested in the region during the reported period. More than 100 private investors and representatives of associations took part in the workshop