Posts

Showing posts from 2018

በሞት የተቀጩትን የሲዳማ ኤጄቶችን ጨምሮ፤ ሌሎች የሲዳማ ዜናዎችን ያካተተ የሲዳማ ቴሌቪዥን ፕሮግራም

Image

የጊዳቦ መስኖ ግድብ ፕሮጀክት ተጠናቆ በተያዘው ወር መጨረሻ ርክክብ ይካሄዳል

Image
ታህሳስ 8/2011 በ2002 ዓ.ም ግንባታው የተጀመረው የጊዳቦ መስኖ ፕሮጀክት ተጠናቆ በተያዘው ወር መጨረሻ ላይ ርክክብ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን አስታወቀ። የጊዳቦ መስኖ ፕሮጀክት በደቡብ ብሔሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦችና በኦሮሚያ ክልሎች የሚገኙ 26 ሺህ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ለማድረግ ታስቦ በ910 ሚሊዮን ብር ወጪ ግንባታው መካሄድ የጀመረው። የጊዳቦ መስኖ ግድብ 63 ሚሊዮን ሜትር ኩብ ውኃ የሚይዝና 11 ሺ ሄክታር መሬት የማልማት አቅም አለው። የኮርፖሬሽኑ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ስራ አስኪያጅ አቶ ጥንፉ ሙጬ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የጊዳቦ መስኖ ግድብን ጨምሮ ኮርፖሬሽኑ ከሚያካሂዳቸው 15 የግንባታ ፕሮጀክቶች መካከል አብዛኞቹ በተያዘው ዓመት ይጠናቀቃሉ ተብሎ ይጠበቃል። በዚህ ዓመት የርብ ግድብን አጠናቆ ያስረከበው ኮርፖሬሽኑ የመስኖ ግድቦች ግንባታ አፈጻጸሙ የተሻለ እንደሆነ አቶ ጥንፉ አስረድተዋል። ኮርፖሬሽኑ የተጓተቱ ፕሮጀክቶች እንዳሉት የተናገሩት አቶ ጥንፉ ከወሰን ማስከበር ጋር በተያያዘ የዘገዩ ፕሮጀክቶች መኖራቸውንም ገልጸዋል። የአርጆ ዴዴሳ ስኳር ፋብሪካ የመስኖ ስራ፣ የወልቃይት ስኳር ልማት መስኖ ስራ እና የቦሌ ቡልቡላ ጥልቅ ውሃ ጉድጓድ የውኃ ቦይ መስመር ግንባታ የዘገዩ ፕሮጀክቶች መሆናቸውን ጠቁመዋል።   የመስኖ ግድቦች መገንባት ብቻውን በቂ አለመሆኑን የገለጹት አቶ ጥንፉ “የግድቦቹ የውኃ ቦይ ግንባታ ተጠናቆ ወደ ልማት መግባት አለባቸው” ብለዋል። የርብ ግድብ 230 ሚሊዮን ሜትሪክ ኪዩብ ውኃ የመያዝና 14 ሺ ሄክታር መሬት የማልማት አቅም ቢኖረውም የውኃ ቦይ ግንባታ ባለመከናወኑ ግድቡ አገልግሎት መስጠት እንዳልቻለ አመልክተዋል። ግድቡን ለአገልግሎት ለማብቃት የሚያ

ደቡብ ግሎባል ባንክ ዓመታዊ ትርፉን በ252 በመቶ በማደሳግ 142 ሚሊዮን ብር አደረሰ

Image
ደቡብ ግሎባል ባንክ በ2010 የሒሳብ ዓመት ከታክስ በፊት 142 ሚሊዮን ብር በማትረፍ ሒሳብ ዓመቱን ማጠናቀቁን አስታወቀ፡፡ ባንኩ በሒሳብ ዓመቱ ከታክስ በፊት ያስመዘገበው የትርፍ መጠን ከባለፈው የሒሳብ ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ252 በመቶ ዕድገት የተመዘገበበት ነው፡፡ ይህ የትርፍ መጠን ዕድገት በኢንዱስትሪው ቀዳሚው ያደርገዋል፡፡ በአዲሱ የሒሳብ አሠራር መሠረት በተዘጋጀው የሒሳብ ሪፖርት ባንኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ትርፉን ከመቶ ሚሊዮን ብር በላይ ማሻገር መቻሉን አመላክቷል፡፡ ባንኩ ቅዳሜ ታኅሳስ 6 ቀን 2011 ዓ.ም. ባካሔደው ጠቅላላ ጉባዔ ላይ እንደተመለከተው ከታክስ በኋላ ያገኘው ትርፍ 106.6 ሚሊዮን ብር መድረሱን የባንኩ ዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀመንበር ገልጸዋል፡፡ ደቡብ ግሎባል ባንክ ኢንዱስትሪውን ዘግየት ብለው ከተቀላቀሉ ባንኮች መካከል አንዱ ሲሆን፣ በ2010 መጨረሻ ላይ የባንኩ ጠቅላላ ሀብት በ58 በመቶ ጨምሮ 3.3 ቢሊዮን ብር ደርሷል፡፡ ባንኩ በሒሳብ ዓመቱ የሰጠው የብድር መጠንም በ101 በመቶ በማደግ 1.58 ቢሊዮን ብር መድረሱም ተጠቅሷል፡፡ ምንጭ 

በ 270 ሚሊየን ብር የተገነባው የሃዋሳ ከተማ ውሃና ፍሳሽ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ተጠናቀቀ

Image
(ኤፍ.ቢ.ሲ)በ270 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባው የሃዋሳ ከተማ የውሃና ፍሳሽ ማስፋፊያ ፕሮጀክት መጠናቀቁ ተገለፀ። ፕሮጀክቱ የሃዋሳ ከተማ ፈጣን ዕድገትና የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ፍላጎትን ለማመጠጠን ሲባል ከዓለም ባንክ ጋር በተደረገ የብድር ስምምነት የተገነባው መሆኑ ነው የተገለፀው። በከተማዋ የሚስተዋለውን የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ያስችላል የተባለው ይህ ፕሮጀክት ፥ የፊታችን ታህሳስ 13 ቀን 2011 ዓ.ም የሚመረቅ መሆኑን ከውሃ፣መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። በሌላ በኩል  በአካባቢው በሚገኘው አምቦ ምንጭ ላይ በተከናወነ የማጎልበት ስራ በሃዋሳ ከተማ የሚገኙ የአዲስ ከተማና የምስራቅ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎችን ንፁህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር መፍታት መቻሉ ተገልጿል። ከምጭ ማጎልበቱ ስራ በተጨማሪም  11 ኪሎ ሜትር ውሃ ማስተላለፊያ ቧንቧ ፣1 ሺህ ሜትር ኩብ ውሃ የሚይዝ ተገጣጣሚ  የውሃ ማጠራቀሚያ እና 2 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የውሃ ማሰራጫ ዋና መስመር ዝርጋት ስራ መከናወኑ ተገልጿል ። በአጠቃላይ ከአምቦ ውሃ ፕሮጀክት በቀን ተጨማሪ 4 ነጥብ 8 ሚሊዬን ሊትር ውሃ የተገኘ ሲሆን ፥ይህም የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎችን ችግር ከመቅረፍ ባሻገር በከተማዋ ውሃ በፈረቃ የሚከፋፈልበትን ሂፈደት ያስቀራል ተብሏል። የአምቦ ምንጭ ፕሮጀክት በ2002 ዓ.ም ተጀምሮ በ2003 ዓ.ም ቢጠናቀቅም፥ በአካባቢው በነበረው ማህበራዊ ችግር ምክንያት ውሃው ጥቅም ላይ የዋለው በ2004 ዓ.ም መሆኑ ይታወሳል። ከዚህ ባለፈም የሃዋሳ ከተማን ውሃ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት በተጨማሪ የፋይናስ ስምምነት 9 ጥልቅ የውሃ ጉድጓዶች በመቆፈር በቀን ተጨማሪ 25 ሚሊየን ሊትር ውሃ ለከተማዋ ተጠቃሚዎች ማዳረ

Ethiopia: ደቡብ - የዶ/ር አብይ ትልቁ ራስ ምታት | Dr Abiy Ahmed } Southern Ethiopia...

Image

የዞኖቹ ክልል የመሆን ጥያቄ ለምን በረታ? እንዴትስ በረከተ?

Image
የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል የመፍረስ አሊያም ቅርጹን የመቀየር እጣ-ፈንታ ገጥሞታል። ቀድሞም በሕዝቦች ይሁንታ አልተዋቀረም በሚባልለት ክልል ለቀረቡት ጥያቄዎች መበርከትና መበርታት ኢሕአዴግ የገባበት የውስጥ ሽኩቻና ግንባሩ ይከተለው የነበረው የማዕከላዊ ዴሞክራሲያዊነት መርኅ መላላት ተጨማሪ ገፊ ምክንያቶች እንደሆኑ ይናገራል። ሙሉ ውይይቱን ለማድመጥ የድምፅ ማዕቀፉን ይጫኑ የኢትዮጵያ ፌድራላዊ ሥርዓተ-መንግሥት ስኬት ተደርጎ በኢሕአዴግ ልሒቃን ይወደስ የነበረው የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል የመፍረስ አሊያም ቅርጹን የመቀየር እጣ-ፈንታ ገጥሞታል። በአስራ አራት ዞኖች እና ሶስት ልዩ ወረዳዎች በተዋቀረው ደቡብ 'ክልል መሆን እንሻለን' የሚል ጥያቄ በተደጋጋሚ እየተደመጠ ነው። ታሪኩን ያጠኑ፤ ፖለቲካውን የተነተኑ እና የገጠመው ፈተና የታያቸው ምሁራን ቀድሞም በሕዝቦች ፍላጎት እና ፈቃድ የተመሠረተ አለመሆኑ ዛሬ ለገባበት ቅርቃር ዋንኛው ምክንያት እንደሆነ ይናገራሉ። ገዢው የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢሕአዴግ) የገጠመው የውስጥ ሽኩቻ በተለይም ይከተለው የነበረው የማዕከላዊ ዴሞክራሲያዊነት መርኅ መላላት ሌላው ገፊ ምክንያት እንደሆነ ባለሙያዎች ይናገራሉ። የዞኖቹ ጥያቄ ቢመለስ ክልሉን በብቸኝነት ላለፉት አመታት የመራው ደኢሕዴን ሊፈርስ፣ በአገሪቱ ፖለቲካ ላይ ይጫት የነበረው ሚናም እንደሚዳከም ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ባለሙያዎች ይናገራሉ። በሳምንቱ እንወያይ መሰናዶ ሲዳማ፣ ወላይታ፣ የከፋ እና የከንባታ ጠንባሮ ዞኖች ያነሱት ጥያቄ በክልሉ እጣ-ፈንታ ላይ የሚያሳድረውን አዎንታዊ እና አሉታዊ ተፅዕኖ ይዳስሳል። በውይይቱ የታሪክ ባለሙያው አቶ አባቡ አሊጋዝ፣ የሕግ እና የፌድራሊዝም

Ethiopia-Kenya high-level cross-border Peace dialogue concludes with an action plan to address ongoing inter-communal conflict along common border

Image
15 December 2018, Hawassa  - The Ethiopia-Kenya high-level cross-border peace dialogue organized by IGAD’s Conflict Early Warning and Response Mechanism (CEWARN) on 14 December 2018 in Hawassa Town, Ethiopia concluded with a joint action plan to address ongoing inter-communal violent conflict along the common border. The dialogue focused on emerging peace, security and development concerns in the Moyale/Moyale and South Omo/Turkana corridors that cover adjoining areas of Oromia and Somali regional states of Ethiopia and Marsabit County of Kenya as well as the Southern Nations Nationalities and Peoples’ Regional State (SNNPRS) of Ethiopia and Turkana County of Kenya respectively. The high-level dialogue was presided over by H.E Zeinu Jamal Ethiopian State Minister of Peace and Mr. Peter K. Thuku (EBS), Head of National CEWERU of Kenya representing Minister of interior and coordination of national government of Kenya as well as Director of CEWARN, Mr. Camlus Omogo. High-level o

ከታሸገ ኮንቴይነር ቡና የተሰረቀባቸው ላኪዎች እየተበራከቱ ነው

Image
የሲዳማ ቡና አምራቾች ኅብረት ሥራ ዩኒየን በበኩሉ ወደ ጀርመን ከላከው 210 ኩንታል ቡና ውስጥ 53.6 ኩንታል እንደጎደለ አስታውቋል፡፡ በተመሳሳይ ወደ ጃፓን ዮኮሐማ ከተማ ለሚስቱቢሺ ከተላከ ቡና ውስጥ 30 ኬሻ፣ አንዳንዶቹም 100 ኬሻ ወይም 60 ኩንታል የጎደለባቸው እንዳሉ ተሰምቷል፡፡ ፋህም የተሰኘው ላኪ ኩባንያ በትንሹ የ8.4 ኩንታል ቡና ጉድለት እንዳጋጠመው ታውቋል፡፡ እስካሁን  ከ150 ኩንታል በላይ የተሰረቁ እንዳሉ ታውቋል በቀላሉ እንዳይከፈት በኮንቴይነር ታሽጎ ወደ ውጭ ከተላከ ቡና ላይ በረቀቀ መንገድ ተከፍቶ ስርቆት የተፈጸመባቸው ላኪዎች ተበራክተዋል፡፡ እስካሁን ስድስት ላኪዎች የሥርቆቱ ሰለባ መሆናቸው ታውቋል፡፡ ሪፖርተር ባደረገው ማጣራት ቴስቲ ኮፊ፣ ሙለጌ፣ አባሃዋ ኩባንያ፣ ሲዳማ ቡና አምራቾች ኅብረት ሥራ ዩኒየን፣ ፋህም ጄኔራል ትሬዲንግና ሌሎችም ወደ ውጭ በኮንቴይነር አሽገው የላኩት ቡና በረቀቀ መንገድ ጎድሏል፡፡ የቴስቲ ኮፊ ኩባንያ ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ ፈይሰል አብዶሽ ዮኒስ፣ ወደ ኮሪያና አውስትራሊያ ከላኩት ቡና ላይ በጠቅላላው 31 ኩንታል እንደጎደለባቸው ተናግረዋል፡፡ ይኸውም በኮሪያ ቡሳን ከተማ ለሚገኘው ደንበኛው ከላኩት አንድ ኮንቴይነር (210 ኩንታል) ቡና ውስጥ 15 ኩንታል ሲወሰድ፣ ወደ ሲድኒ ከላኩት ውስጥ ደግሞ 16 ኩንታል ጎድሎ መገኘቱን ገዥው እንዳሳወቃቸው ገልጸዋል፡፡ የሲዳማ ቡና አምራቾች ኅብረት ሥራ ዩኒየን በበኩሉ ወደ ጀርመን ከላከው 210 ኩንታል ቡና ውስጥ 53.6 ኩንታል እንደጎደለ አስታውቋል፡፡ በተመሳሳይ ወደ ጃፓን ዮኮሐማ ከተማ ለሚስቱቢሺ ከተላከ ቡና ውስጥ 30 ኬሻ፣ አንዳንዶቹም 100 ኬሻ ወይም 60 ኩንታል የጎደለባቸው እንዳሉ ተሰምቷል፡፡ ፋህም የተሰኘው ላኪ ኩባንያ በትንሹ

Ethiopia continues to improve HDI

Image
Health sector improves as education, income lag The 2018 National Development Report from the UNDP has indicated that Ethiopia continues to improve its health system where as indicators such as education and income are said to be behind expectations. The Report which was officially released on December 12, 2018 at Sheraton Addis Hotel focused on the theme, “industrialization with Human Face”. In this regard, it stressed on the point where industrialization should be implemented in a way to improve the lives of Ethiopians and has to be ‘climate smart.’ In the general sense of it, the report indicated that Ethiopia has shown a progress in the past 15 years when it comes to Human Development Index (HDI). According to the report,“The HDI for all regions has increased since the 2012/13 period and the Health SubIndex remains the driver of human development levels across all sub-regional states.” However,“Harari region is the only region to have slipped backwards on the Health

Coffee exporters grapple with cargo pilferage

Image
A systematically orchestrated coffee cargo pilferage destined for export market has become a trend in the export business with at least six exporters reportinga loss of some 150 quintals from sealed containers,  The Reporter  has learnt. Since last month, exporters such as Testi Coffee Trading PLC, Mulege PLC, Sidama Coffee Farmers’ Cooperative Union, Abbahawa Trading PLC, Fahm General Trading PLC and the likes have confirmed loss tonnage in their recent coffee export cargo. FayselAbdosh Yonis, managing director of Testi Coffee PLC, told  The Reporter  that recently his company has received reports of overall loss of 51 bags of coffee (equivalent to 31 quintals)from a 420 quintals coffee shipment staffed and sealed in two containers. According to Faysel, The coffee was destined to reach buyers based in Bussan, South Korea and Sydney, Australia. Fahm Trading, on the other hand,has so far reported a loss of 8.4 quintals from its recent coffee consignment. Similarly, Sidama Coff

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ በሃዋሳ ከተማ ያስገነባውን የመጀመሪያውን አካባቢያዊ የኤሌክትሮኒክ የግብይት ማዕከል የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በዛሬው ዕለት ያስመርቃል፡፡

Image
የኢትዮጵያ ምርት ገበያ በሃዋሳ ከተማ ያስገነባውን የመጀመሪያውን አካባቢያዊ የኤሌክትሮኒክ የግብይት ማዕከል የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በዛሬው ዕለት ያስመርቃል፡፡ ግብይት ማዕከል በሃዋሳ ከተማ መከፈቱ በተለይም ከዲላ፤ከወላይታ ሶዶ፤ ከቡሌ ሆራ ለሚመጡ አርሷደሮችና አቅራቢዎች ለመገበያየት አዲስ አበባ ድረስ በመምጣት በዋናው ማእከል ለመገበያየት የሚያወጡትን ወጪ ያስቀርላቸዋል፡፡ ማዕከሉ የሃዋሳ ከተማ አስተዳደር ለምርት ገበያው በሰጠው 1380 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ ሲሆን ለግንባታው ከ 12 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበታል ከግንባታ በጀቱ 4.8 ሚሊዮን ብሩን የአውሮፓ ህብረት ሲሸፍን 7.76 ሚሊዮን ብር ምርት ገበያው ከፍሏል ። ምንጭ

በኢትዮጵያና ኬንያ ወሰን ሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ የሚመክር መድረክ በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ ነው

Image
ታህሳስ 5፣ 2011 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያና ኬንያ ወሰን ሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ የሚመክር መድረክ በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ ነው። በውይይት መድረኩ ላይ ከሁለቱ ሀገራት የተወከሉ የመንግስት የስራ ሃለፊዎችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ መሆኑም ተገልጿል። ውይይቱ በሁለቱ ሀገራት ወሰን አካባቢ ከጋራ ሃብት አጠቃቀሞ ጋር በተያያዘ የሚነሱ የተለመዱ ግጭቶችን በመፍታት አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ያለመ ነው ተብሏል። ለዚህም ቀደም ሲል በደቡብ ኦሞና ቱርካና ሃይቅ፣ በኢትዮጵያና ኬኒያ ሁለቱም ሞያሌዎች አካባቢ የሁለቱን ሀገራት ህዝቦችን ያሳተፉ ተመሳሳይ ውይይቶች ሲካሄዱ መቆየታቸው ነው የተገለጸው። ከእነዚህ ውይይቶች የመነሻ ግብዓት ተወስዶ በባለሙያዎች በዛሬው ውይይትላይ ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት መሆኑ ተገልጿል። የኢፌዴሪ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ዘይኑ ጀማል እንደገለጹት የኢትዮጵያና ኬኒያ መልካም ጉርብትና በአፍሪካ በአረያነት የሚጠቀስነው ብለዋል። አልፎ አልፎ በሁለቱ ሀገራት ወሰን አካባቢ ከሃብት አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የሚነሱ የተለመዱ ግጭቶች መኖራቸውን በመግለጽ የውይይት መድረኩ ችግሮችን ለመፍታት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል። የሁለቱ ሀገራት መልካም ጉርብትና የበለጠ ለማጠናከርና አልፎ አልፎ የሚከሰቱ ግጭቶችን በባህላዊ መንገድ ለመፍታት ያለመ መሆኑም ተነግሯል። ምንጭ 

Africa: RORI Hotel Hawassa, debuts in Ethiopia

Image
To complement existing hospitality brands in the land of Origin, with flavour and expertise in service delivery, Rori Hotel, Hawassa, a brand new hotel in Ethiopia, has been unveiled. Located in the heart of the beautiful city of Hawassa, the five star hotel is a delight to behold and is closer to the South Nation and Nationalities Peoples Region (SNNPR), state government office. RORI HOTEL incorporates 100 spacious guest rooms appointed as Presidential Suite (Family suites), Suites, Deluxe Room, Twin and Standard rooms. The hotel provides services like; Swimming pool, sauna & steam, Gymnasium, Massage therapy, a well-stocked lobby bar, VIP lounge, Asian Bar and Restaurant, a very well decorated Modern and Traditional restaurants with a wide selection, including special diet menu & wedding and conference halls with flexible accommodation capacity. The hotel also boast of quality services Complimentary Full Breakfast, Free Guestroom Hi-speed WIFI Internet, Free Wi-Fi

Ethiopia: Khat farming threatens food security, biodiversity, women, and agroforestry

Image
Ethiopia: Khat farming threatens food security, biodiversity, women, and agroforestry Southern Ethiopia has long been a stronghold of an ecologically sound version of agriculture, agroforestry, which yields food and medicine crops year round while benefiting a diversity of wild species. In recent decades farmers have moved toward growing only khat, a drug banned in most countries but still legal in Ethiopia and neighboring countries, on their small farms. The transition has led to greater farmer incomes but also declines in food security, biodiversity, soil health, and women’s empowerment. Researchers and activists are advocating for returning such farms at least to modified agroforestry systems of khat intercropped with food crops in the event of a massive crop failure or outright ban of the drug. WONDO GENET, Ethiopia – Agroforestry has been the major agricultural farming system in southern Ethiopia’s Southern Nations, Nationalities and Peoples (SNNP) regional state fo

በአገሪቱ የሚስተዋሉ የጸጥታ ችግርና ስጋት እንዲወገድ ኢትዮጵያውያን ያለ ምንም ልዩነት እንዲሰሩ ተጠየቀ

Image
ሐዋሳ ታህሳስ 3/2011 በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች እየተስተዋለ ያለው የጸጥታ ችግርና ስጋት እንዲወገድ ኢትዮጵያውያን ያለ ምንም ልዩነት እንዲሰሩ የሰላም አምሳደሮች ጠየቁ። ከዘጠኝ ክልሎችና ሁለት ከተሞች አስተዳደሮች የተውጣጡ ሴት የሰላም አምባሳደሮች ቡድን በደቡብ ክልል ሀላባና ሐዋሳ ከተሞች በመገኘት ከኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር ተወያይተዋል፡፡ የቡድኑ መሪ በሰላም ሚኒስቴር የሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች ዳይሬክተር ወይዘሮ አበባ ተገኝ በሀላባ ከተማ ከደቡብ ክልል ሴቶች ማህበር አመራሮች ጋር በተደረገው ውይይት ላይ እንዳመለከቱት ኢትዮጵያውያን በዘር፣ በሃይማኖትና በብሄር ሳይከፋፈሉ  ከችግሮቻቸው ለመውጣት በጋራ መነሳት ይጠበቅባቸዋል። ሰላም ለአገር ልማትና ዕድገት ወሳኝና ቁልፍ መሣሪያ  መሆኑን አመልክተው ሁከትና ግርግር በሚከሰትባቸው አካባቢዎች ከማንም በላይ ተጎጂ የሚሆኑትን ሴቶች ከጉዳት ለመጠበቅ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ብለዋል፡፡ ወንዶች ከማንም በላይ የእናታቸውንና የባለቤቶቻቸውን ሐሳብ እንዲተገብሩ የጠየቁት ወይዘሮ አበባ፣ ሚኒስቴሩ ከሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት ያቋቋመው ቡድን በክልሎች እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በቡድኑ የሐረሪ ክልል ተወካይ ወይዘሮ ገነት አሰፋ እንዳሉት ሴቶች በጸጥታ እጦት ምክንያትም ጉዳት ሰለባ ከመናቸውም በላይ፤ለልጆቻቸውና ለባሎቻቸው ደህንነት በማሰብም በስጋት እንደሚኖሩ ተናግረዋል። ’’እኛ እናቶች ልጅ ወልዶ እስከማሳደግ ባለው ሂደት ለራሳችን ልብሳችንን እየሰፋን ለልጆቻችን አዲስ ገዝተን እያለበስን ከሰው በታች እንዳይሆኑብን ስናስተምር ኖረን መጨረሻ ላይ ግን ዩኒቨርሲቲ ሲሄዱ ሬሳቸው የሚመጣበት ሁኔታ ነው ያለው’’ ብለዋል፡፡ የደቡብ ኢትዮጵያ ሴቶች ማህበር ሊቀመንበር ወይዘሮ