‹‹የአገር ውስጥና የዓለም አቀፍ ገበያ አለመናበብ ለአገሪቱ የቡና ኤክስፖርት ንግድ አለማደግ አንዱ ምክንያት ነው››

ሪፖርተር፡- ለቡና የውጭ ገበያ ከሚከፍለው ዋጋ የኢትዮጵያ አምራቾች ምን ያህል ይደርሳቸዋል?
አቶ ሳኒ፡- ከ35 እስከ 40 በመቶ ቢሆን ነው፡፡  ሌላው በሙሉ ከአርሶ አደሩ በላይ ያሉት የግብይት ሰንሰለቱ ተሳታፊ አካላት የሚቀራመቱት ነው፡፡ ዋናውን ለግብርና (ለቡና) ልማት ዕድገትም ሆነ ለቀጣይነት አርሶ አደሩ ትልቅ ድርሻ የሚገባውና የተጠቃሚነቱን ድርሻ መውሰድ የሚገባው አርሶ አደሩ ነበር፡፡ ስለዚህ ከፍትሐዊነት አንፃር ብዙ መሠራት የሚጠብቀው ነው፡፡ ሌላው በዘመናዊ የግብይት ሥርዓት በግብዓት ተዋንያን ዘንድ መተማመን መፈጠር አለበት፡፡ እርስ በርስ መተሳሰብ መኖር አለበት፡፡ በእኛ ሁኔታ ሲታይ የቡና ዘርፍ ለበርካታ ሕገወጥ ንግድና ዝውውር የተጋለጠ ነው፡፡ ይኼም የሆነበት ምክንያት ወጥ በሆነ መንገድ ሒደቱን ተከታትሎ ራሱን ችሎ የሚመራ ተቋም ባለመኖሩ ነው፡፡ ይህ ምክንያት ታምኖበት ቡናና  ሻይ ባለሥልጣን ተደራጅቷል፡፡ እንግዲህ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ሲደራጅ የግብይት ሥርዓቱንም የመገንባት ተልዕኮ ወስዷል ማለት ነው፡፡ ሦስተኛ እሴት ለሚጨምሩ ኢንዱስትሪዎች የግብርና ምርቶችን ማምረት ብቻ ተጠቃሚ አያደርግም፡፡ እሴት ጨምሮ በተሻለ ዋጋ በመሸጥ የዘርፉ ተዋንያንን ተጠቃሚ ማድረግ ይገባል፡፡ አገሪቷንም ተጠቃሚ ማድረግ ይገባል፡፡ ይህንን ሥራ በማከናወን ሒደት ላይ አሁን ያሉት ተቋማት አሉ? የሉም? ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ይህንን ሁሉ ተልዕኮ ይወስዳል? አይወስድም የሚለው ጥያቄ ይደመጣል፡፡ ቀድሞ የነበሩት ተቋማት አሉ፡፡ በጋራ እየሠራን ነው፡፡ እነዚህን ሥራዎች የሚሠሩ ተቋማት ተጠሪነታቸው በሚኒስቴር ደረጃ ለሦስት አካላት ነው፡፡ ለእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ሚኒስቴር፣ ለንግድ ሚኒስቴርና ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ነው፡፡ እነዚህን ተቋማት ለማቀናጀት የሚያስችል ወደፊት የሕግ ማሻሻያ ተጠንቶ እስኪካሄድ ድረስ፣ የግብርና ምርቶች ኤክስፖርት አስተባባሪ ኮሚቴ ተደራጅቶ እየሠራ ነው፡፡ የግብርና ምርቶች መጋዘን አገልግሎት ድርጅት አገልግሎት የሚሰጠው ለቡና ብቻ አይደለም፡፡ ለሰሊጥ፣ ለጥራጥሬና ለሌሎችም ነው፡፡ ወደፊትም የሚጨመሩ ይኖራሉ፡፡ የምርት ገበያውም ቢሆን የሚያገበያየው ቡና ብቻ አይደለም፡፡ ወደፊት ግን ቡና ራሱን ችሎ በእነዚህ ተቋማት እንዴት ሊመራ ይችላል? የሚለው በጥናት እስኪወሰን ድረስ የማስተባበር ተልዕኮ የተሰጠው ጊዜያዊ ኮሚቴም አለ፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተቋቋመ የግብርና ምርቶች ኤክስፖርት አስተባባሪ ኮሚቴ ነው፡፡
ሙሉ ቃለ ምልልሱን ከሪፖርተር ጋዜጣ ያንቡ

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር