ሀዋሳ 5ኛውን የመላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ታዘጋጃለች

ሀዋሳ 5ኛውን የመላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ታዘጋጃለችግንባታው እየተጠናቀቀ ያለውና 40 ሺ ሰዎችን መያዝ የሚችለው የሀዋሳ ስታዲየም የውድድሩ ድምቀት እንደሚሆን ይጠበቃል፤

8ኛው የፌዴራል ስፖርት ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ከትናንት በስቲያ በተጠናቀቀበት ወቅት በ2008ዓም የሚካሄደውን የ5ኛውን መላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች እቅድ ሰነድ አጽድቋል። ውድድሩን የሀዋሳ ከተማ ታስተናግዳለች።
ጉባኤው ሰነዱን ያጸደቀው ከትናንት በስቲያ በተናቀቀበት ወቅት ነው። በ1999ዓም የተጀመረውና ሁሉንም ክልሎች ባሳተፈ መልኩ የሚካሄደው የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች የኦሎምፒክን ጽንሰ ሃሳብን ይከተላል። በየሁለት ዓመቱ የሚዘጋጀው ይህ ውድድር ብዛት ባለው የስፖርት ዓይነት ብዛት ያላቸውን ስፖርተኞች በማሳተፍም ይታወቃል። በ2008.ም የሚካሄደው የ5ኛው መላ ኢትዮጵያ ጨዋታም በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል በሃዋሳ ከተማ የሚዘጋጅ ይሆናል።
የጨዋታው እቅድ ሰነድም በፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን የስፖርት ተሳትፎና ውድድር ፌስቲቫል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ በቀለ ቀርቧል። በዕቅዱም ላይ በሃዋሳ ከተማ በሚዘጋጀው ውድድር ተጫዋቾችን፣ አሰልጣኞችን፣ የቡድን መሪዎችንና ሌሎችንም ጨምሮ 4150 የሚሆኑ የልኡካን ቡድን አባላት ይሳተፉበታል ተብሎ ይጠበቃል። በዚህም መሰረት ከጥር1እስከ መጋቢት 30 ቀን 2008 .ም ድረስ ክልሎች ዝግጅታቸውንና የተጫዋቾች መረጣቸውን እንደሚጨርሱ በእቅዱ ላይ ተገልጿል።
በዚህም መሰረት የክልሉ መንግስት ባለፈው ዓመት አዘጋጅ ከነበረው የኦሮሚያ ክልል መልካም ተሞክሮዎችን እንዳገኘ ተገልጿል። ክልሉ ለውድድሩ ማካሄጃ የሚያውላቸው የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ዝግጅት ከወዲሁ ተጀምሯል። አዲሱ የሃዋሳ ከተማ ስታዲየም፣ የደቡብ ክልል ፖሊስ ሜዳ እንዲሁም የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሜዳ ለዚህ ውድድር የተዘጋጁ ሲሆን፤ ለቤት ውስጥ ጨዋታዎች ማስተናገጃ የተለያዩ አዳራሾች እንዲሁም የኦሎምፒክ ደረጃውን የጠበቀ የመዋኛ ገንዳ ደግሞ በግንባታ ላይ ይገኛል።
በእቅዱ ላይ 4ኛው መላ አፍሪካ ጨዋታዎች ላይ የታዩ ደካማ ጎኖች ተጠቁመዋል። በውድድሩ ወቅት በተለይ ጎልተው ሲታዩ የቆዩት የስፖርተኞች የስነምግባር እንዲሁም የአድሎና ወገንተኝነት ችግሮች በ5ኛው መላ አፍሪካ ጨዋታዎች ላይ እንዳይደገሙ መሰራት እንዳለበት የምክር ቤቱ አባላት ተናግረዋል።
 ምንጭ፦ ኢዜኣ

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር