4ኛው የጣና ፎረም በባህር ዳር ተጀምሯል፤ መሰል ኣህጉራዊ ጉባዔዎች በሲዳማዋ መዲና ሃዋሳ የምስተናገዱበት ጊዜ መቼ ይሁን?
(ኤፍ.ቢ.ሲ) አራተኛው የጣና ፎረም በባህርዳር ከተማ ተጀምሯል።
ጉባኤው “ሴኩላሪዝም እና ፖለቲካ ጠቀስ የሃይማኖት እንቅስቃሴ” በሚል መሪ ቃል ነው እየተካሄደ ያለው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝን ጨምሮ የማሊ፣ ኬንያ፣ ኡጋንዳ እና ሩዋንዳ መሪዎችን ጨምሮ የታንዛኒያና ቦትስዋና የቀድሞ ፕሬዚዳንቶችና ሌሎች እንግዶች የጉባኤው ተሳታፊዎች ናቸው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም በፎረሙ ላይ የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል።
የተለያዩ ሀገራት ምሁራንም በእምነት ላይ በተመሰረቱ የፖለቲካ እንቅስቃሴዎች ዙሪያ ጥናታዊ ጽሁፎች እየቀረቡ ነው።
በጉባኤው የመላው አለም የሰላም እና ፀጥታ ፈተና የሆነው አክራሪነት ዋና መወያያ ርእስ ይሆናል።
የሴኩላሪዝም ብያኔ፣ ሴኩላሪዝም መከባበርንና ህበረ ብሄራዊነትን ከማስተናገድ አንፃር ያለው ሚና፣ የውጭ ሃይሎች የፖለቲካ ሽፋን ያለው የሃይማኖት እንቅስቃሴን የማራገብ ሁኔታ በጉባኤው ይዳሰሳሉ።
ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት በሚዘልቀው ፎረም የዜጎች የሃገር ፍቅር ግንባታ እና ማህበራዊ ለውጥ በአፍሪካም ይገመገማል።
Comments
Post a Comment