19ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሲዳማ ቡናም ደደቢትን በይርጋለም ይገጥማል

(ኤፍ.ቢ.ሲ) 19ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ እና ነገ በሚደረጉ ጨዋታዎች  ይቀጥላል።
መከላከያ ከአዳማ  ዛሬ ይጫወታሉ።
ነገ የፕሪሚየር ሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮጰያ ቡና 10 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚያደርጉት የሸገር ደርቢም ትልቅ ግምት አግኝቷል።
ቅዱስ ጊዮርጊስ ኔይደር ዶስ ሳንቶስን፤ ኢትዮጵያ ቡና ደግሞ ጥላሁን መንገሻን በተመሳሳይ የውጤት ማጣት ምክንያት ማሰናበታቸው ይታወሳል፡፡
ቅዱስ ጊዮርጊስን ምክትል አሰልጣኝ በነበሩት ፋሲል ተካልኝ እና ዘሪሁን ሸንገታ እየተመራ ታላቁን ድርቢ የሚያደርግ ይሆናል፡፡ 
ኢትዮጵያ ቡናም በተመሳሳይ ምክትል አሰልጣኝ በነበረው አንዋር ያሲን መሪነት ጊዮርጊስን ይገጥማል፡፡ 
ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ18 ጨዋታዎች 35 ነጥብ በመያዝ በሊጉ አናት ላይ ተቀምጧል፡፡
ቡና ደግሞ ከተመሳሳይ 18 ጨዋታዎች በ7 ነጥብ ዝቅ ብሎ በሊጉ አራተኛ ደረጃ ይገኛል፡፡
ፕሪሚየር ሊጉን በሁለተኝነት እየተከተለ ያለው ሲዳማ ቡናም ደደቢትን በይርጋለም ይገጥማል።
የወራጅ ስጋት ያለባቸው ዳሽን እና ሙገር ሲሚንቶ ደግሞ ነገ በአሰላ 9 ሰዓት ላይ የሚገናኙ ይሆናል።
የፊታችን ሰኞ ኤሌክትሪክ በወራጅ ቀጠና ከሚገኘው ወልዲያ ከነማ ሲጫወት፤ ወላይታ ዲቻ ሀዋሳ ከነማን ያስተናግዳል።

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር