የሁለተኛው ዙር ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል: ቅዳሜ በ9 ሰዓት ላይ ሙገር ሲሚንቶ ከመሪው ሲዳማ ቡና ጋር በአሰላ አረንጓዴ ስታዲየም ይጋጠማሉ
የሁለተኛው ዙር ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል።
ሁለተኛው ዙር የመጀመሪያ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ዛሬ ፣ ነገ እና ከነገ ወዲያ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስታውቋል።
በዚህም መሰረት ዛሬ ጎንደር ላይ ዳሽን ቢራ ከወላይታ ዲቻ ሲጫወቱ፥ በተመሳሳይ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ከመከላከያ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ ይገናኛሉ።
በዚህም መሰረት ዛሬ ጎንደር ላይ ዳሽን ቢራ ከወላይታ ዲቻ ሲጫወቱ፥ በተመሳሳይ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ከመከላከያ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ ይገናኛሉ።
ቅዳሜ በ10 ሰዓት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከአዳማ ከነማ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም የሚጫወቱ ሲሆን፥ 9 ሰዓት ላይ ሙገር ሲሚንቶ ከመሪው ሲዳማ ቡና ጋር በአሰላ አረንጓዴ ስታዲየም ይጋጠማሉ።
ታላቁ የአዲስ አበባ ደርቢ ጨዋታ እሁድ በ9 ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮጵያ ቡናን ያፋልማል።
ደደቢት በሁለተኛ ዙር በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ከናይጄሪያ ዋሪ ዋልቭስ ክለብ ጋር በዚህ ሳምንት ባለበት ጨዋታ ምክንያት ከወልዲያ ከነማ በወልዲያ ላይ የሚያደርገው ጨዋታ ወደ መጋቢት 13 ቀን 2007 ዓ.ም እንዲራዘም ተወስኗል፡፡
የመጀመሪያው ዙር ፕሪሚየር ሊግ ደረጃ ሲዳማ ቡና በ27 ነጥብ በአንደኝነት ሲመራ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ በ25 ነጥብ በሁለተኝነት፣ ወላይታ ዲቻ በ23 ነጥብ ሶስተኛ እንዲሁም ኢትዮጵያ ቡና በ21 ነጥብ አራተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
Comments
Post a Comment