በሁለተኛው መላው የደቡብ ክልል የትምህርት ቤቶች የስፖርት ውድድር የሃዋሳ ከተማ አስተዳደር ሲዳማ ዞንን ሁለት ለባዶ አሸነፈ

ሁለተኛው መላው የደቡብ ክልል የትምህርት ቤቶች የስፖርት ውድድር ትናንት ተጀመረ
ሁለተኛው መላው የደቡብ ክልል የትምህርት ቤቶች የስፖርት ውድድር ተጀምሯል። ለ15 ቀናት በሚቆየው በዚሁ ውድድር ከ14 ዞኖች፣ 4 ልዩ ወረዳዎችና ሃዋሳ ከተማ አስተዳደር ስር ከሚገኙ ትምህርት ቤቶች የተወጣጡ አንድ ሺህ 780 ተማሪዎች በመሳተፍ ላይ ሲሆኑ ከመካከላቸውም 783 ሴቶች ናቸው፡፡
ተሳታፊዎቹ በቆይታቸው በእግር ኳስ፣ በአትሌቲክስ፣ በመረብ ኳስና ጠረጴዛ ቴንስን ጨምሮ በ13 የስፖርት አይነቶች ውድድር ያካሂዳሉ፡፡
ውድድሩ በሃዋሳ ሜዳ፣ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ፣ ግብርና ኮሌጅና  ሌሎች ማዘውተሪያ ቦታዎች ላይ የሚደረግ ይሆናል።
በውድድሩ የተሻሉና ጥሩ ተፎካካሪ የሆኑ ተማሪዎችን በመመልመል በመጋቢት ወር በባህርዳር ከተማ በሚደረገው ሀገር ዓቀፍ የተማሪዎች ስፖርት ውደድር ላይ  ክልሉን ወክለው እንዲሳተፉ ይደረጋል ብለዋል።
በሃዋሳ ስታዲየም በተጀመረው የመክፈቻ ስነስርአት ላይ የተለያዩ አዝናኝ የጅምናስቲክ ትርኢቶች የቀረቡ ሲሆን በወንዶች በተደረገ የእግር ኳስ ግጥሚያ የሃዋሳ ከተማ አስተዳደር ሲዳማ ዞንን ሁለት ለባዶ አሸንፏል፡፡
- See more at: http://www.ena.gov.et/index.php/politics/item/2079-2015-02-18-16-27-42#sthash.zZWTEekO.dpuf

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር