መድረክ በሃድያ ዞን ሁለት ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍ አካሄደ
የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ፓርቲ በሃድያ ዞን ሁለት ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍ አካሄደ።
ፓርቲው ትናንት እና ዛሬ ሰለማዊ ሰልፉን ያካሄደው በሆሳእና ከተማ እና በምስራቅ ባዳዋቾ ሾኔ ከተሞች ነው።
የመድረክ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደተናገሩት፥ በሁለቱ ከተሞች በተካሄደው ሰልፍ የፓርቲው አመራሮች፣ አባላት እና ደጋፊዎች ተገኝተዋል።
ሊቀመንበሩ ሰልፉ በፀጥታ ኃይሎች ትብብር ያለምንም ችግር መከናወኑን ተናግረዋል።
Read more: ኤፍ.ቢ.ሲ
Comments
Post a Comment