ሲዳማ ቡና መከላከያን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናከረ

አዲስ አበባ ታህሳስ 25/2007 ዛሬ በተካሄደው የ10ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ የእግር ኳስ ጨዋታ ሲዳማ ቡና መከላከያን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናክሮ ቀጥሏል።
ሲዳማ ቡና ከመጀመሪያው ከዕረፍት በፊት ያገኘውን የቅጣት ምት በቀጥታ ወደ ግብ በመለጥ 1 0 አሸንፏል።
ከጨዋታው በኋላ አሰልጣኞች አስተያየታቸውን የሰጡ ሲሆን የመከላከያው አሰልጣኝ ገብረመድህን ኃይሌ "ሜዳውና አንድ ስህተት ቀላል የማይባል ችግር ላይ ጥሎናል፤ ዋጋም  አስከፍሎናል" ብሏል።
የሲዳማ ቡናው አሰልጣኝ ዘላለም ሽፈራው በበኩሉ "የመልሶ ማጥቃት አጨዋወት ስልትን ተግብረን ኳስን ይዞ የሚጫወተውን መከላከያ አሸነፍን መውጣታችን ትልቅ ውጤት ነው" ሲል በውጤቱ መደሰቱን ገልጿል።
አሰልጣኝ ዘላለም "በቀጣይ ዋንጫ ወደ ማንሳት እንድናነጣጠር አድርጎናል ውጤቱ" በማለት ውጤቱ የፈጠረለትን ተጨማሪ ተስፋ የገለጸው።
አሰልጣኙ ይህን ያለው ጥቂት ልምድ ባላቸውና በበርካታ ወጣቶች ስብስብ የተዋቀረው ቡድኑ ውጤታማ ካደረገው በኋላ ነው።
"ጥሩ ተፎካካሪ ሆኖ መጨረስ እንጂ ዋንጫን አላሰብነውም ነበር አሁን ግን ይህን ማድርግ እንችላለን" በማለትም ቀጣይ ግቡን አመላክቷል።
ሁለቱም አሰልጣኞች የመጫወቻ ሜዳው ውጤት ላይና ተጨዋቾች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንዳለው ገልጸዋል።
በአበበ ቢቂላ ስታዲየም አራት የሚደርሱ ተጨዋቾች ያለ ተቃራኒ ተጨዋች ንክኪ ሜዳው ባለው አስቸጋሪ ተፈጥሮ ለጀርባ፣ ለጭንና ለባት ጡንቻ ጉዳት ሲጋለጡ ተስተውለዋል።
ሜዳው አስቸኳይ መፍትሄ የሚያሻው ቢሆንም በፍጥነት ግን መፍታት እንደማይቻል ነው ከፌዴሬሽኑ የተገኘ መረጃ ያመላከተው።
ብሔራዊ ስታዲየሙ 12ኛውን የአፍሪካ ወጣቶች የአትሌቲክስ ሻምፒዮናን ከማስተናገድ ጋር ተያይዞ እድሳት ላይ በመሆኑ ነው ውድድሩ ወደ አበበ ቢቂላ ስታዲየም እንዲዛወር የተደረገው።
ፕሪሚዬር ሊጉ ነገ በአበበ ቢቂላ ስታዲዮምና በክልል ከተሞች ቀጥሎ ይካሄዳል።

- See more at: http://www.ena.gov.et/index.php/sport/item/926-2015-01-04-04-51-22#sthash.qAOmWhuF.dpuf

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር