ጠንካራዎቹ የደቡብ ክልል ክለቦች

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከሚወዳደሩ 14 ክለቦች መካከል የደቡብ ክልል አራት ክለቦችን በማሳተፍ ከክልሎች ቀዳሚው ነው። ክልሉ ከሚወከልባቸው አራት ክለቦች መካከል ሶስቱ ከመሪዎቹ መካከል የሚመደቡ ናቸው። ሃዋሳ ከነማም ቢሆን ለጊዜው በደረጃው ግርጌ አካባቢ መሰንበቻውን ያደረገ ቢሆንም ካለው የቡድን ስብስብና የቆየ ታሪክ በመነሳት በቅርቡ ወደ መሪዎቹ የመመለስ እድል እንዳለው በርካቶች ግምታቸውን ይሰጣሉ። የክልሉ ክለቦች ከሰበሰቡት ነጥብ በተጨማሪ በፕሪሚየር ሊጉ ትልቅ ልምድና ውጤት ያላቸውን ለቦች ሳይቀር ማሸነፍ ችለዋል። ለአብነት ያህል የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና መከላከያን፣ ደደቢትንና ኢትዮጵያ ቡናን ሲያሸንፍ አርባ ምንጭ ከነማ በበኩሉ በሜዳው ቅዱስ ጊዮርጊስንና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን አሸንፎ ከሜዳው ውጭ ደግሞ ከደደቢትና መከላከያ ጋር ነጥብ ተጋርቶ ተመልሷል። ወላይታ ድቻም ተመሳሳይ ገድል አለው።  
ተጨማሪ ለማንበብ

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር