በዚህ ሳምንት የፕሪሚየር ሊግ ውድድር ሲዳማ ቡና ወደ ኣዲስ ኣበባ ተጉዞ ንግድ ባንክን ይገጥማል
ፎቶ ከ soccerethiopia.net |
በአስደናቂ ጉዞ ላይ ያለው ሲዳማ ቡና በዚህ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ወደ ኣዲስ ኣበባ ተጉዞ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ይገጥማል። ሁለቱ ክለቦች በምመጣው እሁድ ከቀኑ ኣስር ሰዓት ላይ በኣበበ ቢቂላ ስታዲዬም ውድድራቸውን እንደሚያደርጉ ታውቋል።
የሲዳማ ቡና ባለፈው ሳምንት ይርጋለም ከተማ ላይ ኢትዮጵያ ቡናን ኣስተናገደው 1-0 አሸንፎ ያሸነፈ ሲሆን፤ የሲዳማ ቡናን የድል ግብ ያስቆጠረው ኬንያዊው አጥቂ ኤሪክ ሙራንዳ መሆኑ ይታወሳል፡፡
Comments
Post a Comment