Posts

Showing posts from June, 2014

የመንግስት ሰራተኞች የደሞዝ ጭማሪ መጠን እስካሁን አልታወቀም

በየ3 አመቱ የደሞዝ ጭማሪ ሊደረግ ይችላል ከመጪው ሐምሌ ወር ጀምሮ ለመንግስት ሠራተኞች እንደሚጨመር የተነገረው የደሞዝ መጠን እስካሁን በይፋ አልተገለፀም፡፡   በሌላ በኩል ከአሁን በኋላ በየሦስት አመቱ ለመንግስት ሠራተኞች የደሞዝ ጭማሪ ሊደረግ እንደሚችል ምንጮች ጠቁመዋል፡፡  በሲቪል ሠርቪስ ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ጌታቸው አብዲሣ፤ በቅርቡ መንግስት ይጨመራል ብሎ ከሰጠው መረጃ ውጪ በምን ያህል ፐርሰንት እንደሚጨመር መረጃ አልደረሰንም ብለዋል፡፡  ለመንግስት ሠራተኞች ለመጨረሻ ጊዜ ደሞዝ የተጨመረው በታህሳስ ወር 2003 ዓ.ም ሲሆን በወቅቱ ከ38.75 በመቶ እስከ 44.71 በመቶ የሚደርስ ጭማሪ መደረጉ የሚታወስ ሲሆን አሁን ከዚያ በላይ የደሞዝ ጭማሪ እንደሚጠበቅ በግል ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ መምህር አቶ መስፍን ይልማ ግምታቸውን ሰንዝረዋል። የደሞዝ ጭማሪው በተለይ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የመንግስት ደሞዝተኞችን ተጠቃሚ ማድረግ እንዳለበት ተናግረዋል - ምሁሩ፡፡  የደሞዝ ጭማሪ ስሌቱ አለመታወቁ ትንታኔዎችን ለመስጠት ያስቸግራል ያሉት መምህሩ፤ እስከዛሬ በመንግስት በኩል የሚደረጉ የደሞዝ ጭማሪዎች የሠራተኛውን ፍላጐት አርክተው አያውቁም፤ ይኸኛውም ጭማሪ የተለየ ነገር ይዞ አይመጣም ብለዋል፡፡  ባለፉት አምስት ዓመታት በፓርላማ ብቸኛ የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካይ የሆኑት የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ በበኩላቸው፤ የደሞዝ ጭማሪው አስፈላጊና ወቅታዊ መሆኑን ጠቅሰው፤ ጭማሪው አንዲት ሣንቲም እንኳ ቢሆን በሠራተኛው ህይወት ላይ ለውጥ ባያመጣም ትርጉም አለው ይላሉ፡፡  መንግስት መቼውንም ቢሆን የሠራተኛውን ፍላጐት ሊያሟላ የሚችል ደሞዝ የመጨመር አቅም አይኖረውም ያሉት የፓርላማ አባሉ፤ አንድ የመንግስት ሰራተኛ የሚመራው ኑሮ ሊስትሮ ከሚሰራ ሰው

የዲያስፖራውን ሙሉ መረጃ አጠናቅሮ መያዝ የሚያስችል አሰራር መዘርጋት ይገባል-ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

Image
አዲስ አበባ ሰኔ 23/2006 ዲያስፖራው በአገሩ የልማት እንቅስቃሴ ላይ በስፋት እንዲሳተፍና በሚኖርበት አገር ሁሉ መብቱን ማስከበር እንዲችል የዲያስፖራውን ሙሉ መረጃ አጠናቅሮ መያዝ የሚያስችል አሰራር መዘርጋት እንዳለበት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከአለም አቀፍ የስደተኞች ተቋም ጋር በመተባበር ከ20 በላይ ከሚሆኑ ኤምባሲዎች ለተውጣጡ የኢትዮጵያ አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች "ዲያስፖራውን ማወቅ" በሚል ርዕስ በአዲስ አበባ ስልጠና እየሰጠ ነው። በዚሁ ወቅት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ደዋኖ ከድር እንደተናገሩት የዲያስፖራውን ሙሉ መረጃ በማወቅ በአገሩ ልማት ላይ በስፋት እንዲሳተፍ ማድረግ ይገባል። ከአሁን በፊት የነበረው አሰራር የዲያስፖራውን መገኛ ቦታ ብቻ በማወቅ ላይ የተመሰረተ እንደነበር ጠቁመዋል፡፡ አቶ ደዋኖ እንዳሉት ዲያስፖራውን ከአገሩ ልማት ጋር ማቆራኘት እንዲቻል የአሁኑ ስልጠና ጥሩ ተሞክሮ ያላቸው አገሮችን ልምድ ያካተተ እንዲሆን ተደርጓል። ለአሁኑ ስልጠና እንዲሳተፉ የተጋበዙ ዲፕሎማቶች ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በስፋት ከሚገኙበት አገራት እንደመሆኑ መጠን ስልጠናውን ጨርሰው ወደመጡባቸው አካባቢዎች ሲመለሱ ዲያስፖራውን በማስተሳሰሩ ረገድ ብዙ ስራ ይጠብቃቸዋል ብለዋል። የአለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት ተልዕኮ የኢትዮጵያ ኃላፊ ሚስተር ጆሲያህ ኦጊና እንዳሉት ድርጅቱ የምሁራንን ፍልሰት ለመግታትና የስደተኞችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከመንግስት ጎን ይሰለፋል።   ከውጭ ለሚመለሱ ኢትዮጵያውያንም አጫጭር ስልጠናዎችን በመስጠት በዘላቂነት ራሳቸውን እንዲችሉ በማገዝና ጊዜያዊ የቁሳቁስ አቅርቦት በማድረግ ድጋፍ እንደሚያደርግም ገልፀዋል። ዲያስፖራው ለአገሩ ልማት

Your Fair Trade Coffee and Quinoa Aren’t Improving Farmers’ Lives

Image
When confronted with the ability to make the “ethical” choice at the grocery store, picking up a bag of Fair Trade certified coffee seems like a no-brainer. With a commitment to worthy goals like reducing poverty, empowering women, and supporting education, Fair Trade products appear to put the power of creating a better world in the hands of the purchaser. But the impact may not be a benefit for the poorest workers, and like other food trends, could be negatively impacting the lives of the people producing some of our foods. A recently released four-year study,  Fairtrade, Employment and Poverty Reduction in Ethiopia and Uganda , found that Fair Trade certification does not have the positive impact on producers consumers may believe it does. For the report, the University of London researchers collected data from Ethiopia and Uganda in regions where coffee, tea, and flowers are produced. It found that the workers involved in Fair Trade production had very low wages, and they did

Speech Recognition System: Speaker Dependent Recognizer for Sidama Language

Image
by  Abdella Kemal Mohammed   (Author) Speech recognition systems have been applicable in wide areas as various speech recognition methodologies, techniques and tools have been developed and implemented to generate a natural and intelligible speech. In this regard, this work attempts the possibility of developing a prototype speech recognition system for Sidama language using Hidden Marcov Model. The study has conducted extensive study on the language features, the components, speech recognition tools; the techniques used in speech recognition design, and identified those component that are dependent on the characteristics of language. Finally this work has showed a working prototype speech recognizer for the language, tested the performance of the system and compared its accuracy, and recommended measures for similar researches and projects. This work, therefore, will be useful to researchers, Speech application developers, Educators and other individuals or institutions working on

የቡና ንግድ ቀይ መብራት በርቶበታል

Image
ሚኒስትሮች ተሰብስበዋል፡፡ የሚኒስትሮቹ ጠቅላይ አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ስብሰባውን ይመራሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ ሚኒስትሮችና ከዚያ በታች በተዋረድ የሥልጣን ዕርከን ላይ የሚገኙ 37 ሹማምንት ለስብሰባው ሲጠበቁ 25ቱ ተገኝተዋል፡፡ በሦስት ሚኒስቴሮች የኤክስፖርት አፈጻጸም ላይ በብሔራዊ ኤክስፖርት አስተባባሪውና የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ሚኒስትር በአቶ አርከበ ዕቁባይ (የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ይዘዋል) ጠሪነት ለአምስት ሰዓት የዘለቀ ስብሰባ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት ተካሂዷል፡፡ ስብሰባው ከጥቂት ወራት በፊት የተካሄደ ነው፡፡ ከመነጋገሪያ ነጥቦቹ አንዱ የሆነው የንግድ ሚኒስቴር የኤክስፖርት አፈጻጸም ነበር፡፡ ከዚህም ውስጥ ቡና ላይ ትኩረት አድርጎ፣ ሌሎች የግብርና ምርቶችንም ተመልክቷል፡፡ ‹‹በንግድ ሚኒስቴር ክትትል የሚደረግባቸው የግብርና ምርቶች የኤክስፖርት ዕቅድ አፈጻጸም በተያዘው ዕቅድ መሠረት ለማሳካት የተከተልነው የአሠራር ሥርዓትና የማኔጅመንት አመራር ለውጥ ያላመጣው በምን ምክንያትን እንደሆነ አጽንኦት ተሰጥቶት ቢታይ፤›› የሚል መነሻ ያሰፈረው የመወያያ አጀንዳ፣ ከዚህ ቀደም በኤክስፖርት ብሔራዊ አስተባባሪ ኮሚቴው በኩል የተሰጡ ማሳሰቢያዎችና የሥራ መመርያዎች ብዙም ለውጥ እንዳላመጡ ይገልጻል፡፡  ከቀረቡት ዝርዝር ነጥቦች መካከል ለአብነት መጥቀስ ቢያስፈልግ፣ ከዚህ ቀደም ኮሚቴው የኢትጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን፣ የንግድ ሚኒስቴር፣ የግብርና ሚኒስቴርና የፀጥታ አካላት በጋራ ተቀናጅተው በተለይ የቡና ኤክስፖርት ዕቅድ አፈጻጸምን ለማቀላጠፍ ይቻል ዘንድ፣ ቡና በብዛት ወደ ምርት ገበያ እንዲገባ በማድረግ የአቅርቦት መጠኑ እንዲጨምር የሚል መመርያ ሰጥቶ እንደነበር ያስታውሳል፡፡ ሆኖም ግን የተለየ ለውጥ አለመምጣቱን

በግብርና ምርቶች ላይ እሴት ጨምሮ መላክ የሚያስችል የተቀናጀ የግብርና ኢንዱሰትሪ ፓርኮች ሊመሰረቱ ነው

Image
 በግብርና ምርቶች ላይ እሴት ጨምሮ መላክ የሚያስችል "የተቀናጁ የግብርና ኢንዱሰትሪ ፓርኮች" ለመመስረት የሚያስችል ጥናት በማካሄድ ላይ እንደሆነ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ገለፀ። ሚኒስትር ዲኤታው ዶክተር መብራቱ መለስ የግብርና ምርቶችን እሴት ጨምሮ ወደ ውጭ ገበያ ማቅረብ እንደሚያስፈልግና ለዚህም እሴት ጨምረው መላክ የሚያስችሉ ኩባንያዎች ማቋቋም መሰረታዊ ነገር መሆኑን ተናግረዋል። ሚኒስትሩ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደተናገሩት ፓርኮቹ የግብርና ምርት በብዛት የሚገኝባቸው ቦታዎችን በጥናት በመለየት የሚከናወኑ ናቸው ። የግብርና ምርቶችን እሴት ጨምሮ ለአለም ገበያ ባለማቅረብ የተነሳ አገሪቱ ከፍተኛ የሆነ የውጭ ምንዛሬ እያጣች ነው ያሉት ሚኒስትሩ በቀጣይ ግን ፓርኮችን ገንብቶ ኢንዱስትሪዎች በማቋቋም  ከፍተቱን ለሞምላት እንደሚጥሩ ተናግረዋል። የሚቋቋሙት ኢንዱሰትሪዎች የገበሬውን የግብርና ምርት በስፋት መጠቀም መቻላቸው አርሶ አደሩ ዘላቂና አስተማማኝ የሆነ የገቢ ምንጭ እንዲኖረው እንደሚያደርግና የአርሶ አደሩን ህይወት መቀየር እንደሚችሉ አስረድተዋል። በሚቋቋሙት ኢንዱስትሪዎችም ከፍተኛ የስራ እድልና የኢንተርፕራይዞች መፈጠር እንደሚያስፋፋ ጨምረው ተናግረዋል። ሚኒሰትሩ እንደተናገሩት "የተቀናጁ የግብርና ኢንዱሰትሪ ፓርኮች"  በስኳር ማምረቻ አካባቢዎች፣ የፍራፍሬና የአትከልት ምርት በስፋት በሚኖርባቸው፣ የሰሊጥ እንዲሁም የቡና ምርቶች በሚበዙባቸው ቦታዎች ላይ ይጀመራሉ። በሚቀጥለው የበጀት አመት በሚጠናቀቀው የእድገትና የትራንስፎርሜሺን እቅድ ላይ መጀመር እንዲቻል የጥናት ስራው በመፋጠን ላይ ይገኛል ያሉት ሚኒሰትሩ በሚቀጥለው የእቅድ ዘመን ግን በስፋት በመላው አገሪቱ እንደሚተገበሩ አረጋግጠዋል።

ሁለት የሃዋሳ ከተማ ተጫዋቾችን የያዘው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከቱርክ አቻው ጋር የወዳጅነት ግጥሚያ እንዲያደርግ መታቀዱን ተሰማ

Image
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2006 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከቱርክ አቻው ጋር የወዳጅነት ግጥሚያ እንዲያደርግ መታቀዱን አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ አስታወቁ። አሰልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ በዛሬው እለት ስለቡድኑ አጠቃላይ እንቅስቃሴ መግለጫ በሰጡበት ወቅት ነው ይህን ያሉት። አሰልጣኙ መግለጫ ከሰጡባቸው ዋነኛ ሀሳቦች መካከል ፥ የመረጧቸው 38 ተጨዋቾች የዝግጅት ሂደት ምን ይመስላል የሚለው ይጠቀሳል። በተጨማሪም ዋነኛ አላማቸው በ2015 በሞሮኮው የአፍሪካ ዋንጫ መሳተፍ እንደሆነ በመግለፅ፥ አልጄሪያን ከመግጠማቸው በፊትም የወዳጅነት ጨዋታ ወደ ቱርክ አቅንተው ለመጫወት እንደታሰበ አስረድተዋል። አብዛኛውን ተጨዋቾች በደንብ ስለሚያውቋቸው ም/አሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ እና ዳንኤል  ፀሀዬን እኔው እራሴ ምክትሎቼ አድርጌ መርጫቸዋለው ብለዋል በመግለጫቸው ላይ። ከ20 አመት በታች የሚገኙ ተጨዋቾች የሚሳተፉበት  ክለቦች ሊግ በአገር ውስጥ ሊኖር እንደሚገባ እና  ተተኪዎችን ለማፍራት ከ14  ፣ 17 እና ከ20 አመት በታች ተጨዋቾች ላይ መሰራት እንደሚኖርበትም ነው የገለፁት። ዜናው የፋና ነው

በስነ ምግባር የታነጸ ዜጋ በመፍጠር ፆታዊ ጥቃትን ለመከላከል የሃይማኖት ተቋማት መከሩ

Image
በስነ ምግባር የታነጸ ዜጋ በመፍጠር ፆታዊ ጥቃትን ለመከላከል በሃይማኖት ተቋማት ሚና ላይ የተዘጋጀ ክልል አቀፍ የሃይማኖት ተቋም የሁለት ቀን የምክክር ጉባኤ የአቋም መግለጫ በማውጣት ትናንት ማምሻውን ተጠናቋል፡፡ ከተሳታፊዎቹ መከካል የደቡብ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሰብሳቢ የሲዳማ፣ የቡርጂና ጌድኦ ሀገር ስብከት ስራ አስኪያጅ ሊቀ ጉባኤ አባ ሀብተማርያም ገብረመስቀል እንደተናገሩት ያለስነ ምግባር የሚካሄድ ማንኛውም ስራ ሂደቱ አስቸጋሪ ውጤቱም አስከፊ በመሆኑ በስነ ምግባር የተገነባ ዜጋ ለመፍጠር ከሃይማኖት ተቋም አባቶች ብዙ ይጠበቃል፡፡ የአከባቢን ስነ ምህዳር በመጠበቅ ለሰው ልጆች ምቹና ተስማሚ የመኖሪያ ስፍራ ለመፍጠር፣ልማትን ከሙስና ማጽዳት፣ ስራን ከስህተትና ከጉዳት ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ሁሉ የሃይማኖት አባቶችና ተከታዮቻቸው የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ሊያደርጉ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡ ጉባኤው በስነ ምግባር የታነፁ ዜጎችን ለማፍራትና በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ፆታዊ ጥቃት እንዲሁም ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለማስወገድ ሁሉም የሃይማኖት ተቋማት ሚና ምን መሆን እንዳለበት ግልፅ አቅጣጫ ያሳየ ነው ብለዋል፡፡ የደቡብ ክልል የእስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዜዳንትና የሃይማኖት ተቋማት ምክትል ሰብሳቢ ሀጂ ሚፍታህ ሰኢድ በመከባበርና በሰላም አብሮ በመኖር የሚያምኑ፣በልማትና ዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሂደት ሀገራዊ ሃላፊነት መሸከም የሚችሉ ዜጎችን የማፍራት ጉዳይ ልዩ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ብለዋል፡፡ ጠንካራ የስራ ባህል ያላቸው፣ በራሳቸው የሚተማመኑና ከማንኛውም ጥገኛ ልማድ ነፃ የሆኑ ፣ ኃላቀር አስተሳሰቦችን በመዋጋት እውቀትን የመሻት ዝንባሌ የተላበሱ ወጣቶችን ለማፍራት ከሃይማኖት ተቋማት ብዙ የሚጠበቅ በመሆኑ ጠንክረው

የሻምበል አበበ ብቂላ ማራቶን በሐዋሳ ተካሄደ

Image
ዜናው የሪፖርተር ጋዜጣ ነው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በየዓመቱ የሚያዘጋጀው የሻምበል አበበ ብቂላ ማራቶን ባለፈው እሑድ በሐዋሳ ከተማ ሲካሄድ በወንዶች የፌዴራል ፖሊስ ስንታየሁ ለገሰ፣ በሴቶች ደግሞ የመከላከያዋ አፀደ ባይሳ አሸናፊ ሆነዋል፡፡ በ1956 በሮም፣ እንዲሁም በ1960 ዓ.ም. በቶኪዮ በተዘጋጁት የኦሊምፒክ ውድድሮች በማራቶን የወርቅ ሜዳሊያዎችን በማስመዝገብ ከአገሩ አልፎ አፍሪካን እንዳኮራ የሚነገርለት ሻምበል አበበ ብቂላ አሁንም ድረስ በስመ ገናናነቱ ይጠቀሳል፡፡ በተለይ ደግሞ በሮም አውራ ጎዳናዎች 42 ኪሎ ሜትር ከ195 ሜትር የሚሸፍነውን ማራቶን በባዶ እግሩ ሮጦ የወርቅ ሜዳሊያ ያስመዘገበበት ታሪኩ በአራት ዓመት አንድ ጊዜ እየተዘጋጀ ዛሬ ላይ ለደረሰው ዘመናዊ ኦሊምፒክ ተምሳሌት እንደሆነም ይገኛል፡፡ ‹‹ኢትዮጵያና አትሌቲክስ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታ›› ሆነው እንዲቀጥሉ ፈር ቀዳጅ መሆኑ ለሚመገርለት ሕያው አትሌት፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በስሙ የማራቶን ውድድር ማዘጋጀት ከጀመረ ሦስት አሠርታት አስቆጥሯል፡፡ በዚሁ መሠረት ባለፈው እሑድ ሰኔ 15 ቀን 2006 ዓ.ም. በሐዋሳ ባከናወነው ማራቶን በወንዶች ከፌዴራል ፖሊስ ስንታየሁ ለገሰ ርቀቱን 2 ሰዓት፣ 13 ደቂቃ፣ 28 ሰከንድ፣ በሆነ ጊዜ አጠናቆ አንደኛ ሲወጣ፣ ረጋሳ ምንዳዬ ከኦሮሚያ 2 ሰዓት፣ 13 ደቂቃ፣ 30 ሰከንድ ከፌዴራል ፖሊስ ገዛኸኝ አበራ 2 ሰዓት፣ 13 ደቂቃ፣ 32 ሰከንድ በመግባት ሁለተኛና ሦስተኛ ሆነዋል፡፡ በሴቶች ከመከላከያ አፀደ ባይሳ 2 ሰዓት፣ 45 ደቂቃ፣ 60 ሰከንድ፣ እንዲሁም ከዚሁ ክለብ እመቤት ኢተአ 2 ሰዓት፣ 47 ደቂቃ፣ 25 ሰከንድ ስትወጣ፣ በግል የቀረበችው ሻሾ     2 ሰዓት፣ 47 ደቂቃ፣ 26 ሰከንድ ሦስተኛ በ

የደመወዝ ጭማሪው የዋጋ ንረት እንደማያስከትል ግልጽ መደረግ አለበት!

Image
የዋጋ ንረትን በተመለከተ ሰሞኑን ሁለት ተቀራራቢ የሆኑ ክስተቶች ተሰምተዋል፡፡ የመጀመሪያው የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ባለሥልጣን የግንቦት ወር 2006 ዓ.ም. የዋጋ ንረትን በማስመልከት ያወጣው ሪፖርት ሲሆን፣ ሁለተኛው መንግሥት የዋጋ ንረትን በማይቀሰቅስ ሁኔታ ለመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ለማድረግ መወሰኑ ነው፡፡ ይህ ውሳኔ ለሠራተኛው ሕዝብ መልካም ብሥራት ነው፡፡ ነገር ግን የተጠና መሆን አለበት፡፡ የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ባለሥልጣን ሪፖርት እንደሚያሳየው በግንቦት ወር የአገሪቱ አጠቃላይ የዋጋ ንረት 8.70 በመቶ በማስመዝገብ፣ በመላ አገሪቱ ባለፉት 15 ወራት የዋጋ ንረቱ በነጠላ አኃዝ እንደቀጠለ ነው፡፡ የዋጋ ንረቱ እ.ኤ.አ. ከማርች 2013 ጀምሮ በነጠላ አኃዝ መቀጠሉን ለመንግሥት እንደ ስኬት እንደሚታይ ሪፖርቱ ያብራራል፡፡ የዋጋ ንረቱ በነጠላ አኃዝ መቀጠሉ አዎንታዊ ገጽታ ነው፡፡ ይሁንና መንግሥት ከሐምሌ ወር ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ እጨምራለሁ ሲል ያቀረበው ታሳቢ ጭማሪው የዋጋ ንረት የማያስከትል መሆኑን ነው፡፡ ጥያቄ የሚነሳውም እዚህ ላይ ነው፡፡ የደመወዝ ጭማሪ ሲደረግ የዋጋ ንረት እንደማይባባስ የሚደረገው ምን ዓይነት ዕርምጃዎችን ወይም መለኪያዎችን በማሰብ ነው? ለመንግሥት ሠራተኞች የሚደረገው የደመወዝ ጭማሪ ኢኮኖሚው ተረጋግቶ መቀጠል በሚችልበት ሁኔታ ተጠንቶ ተግባራዊ እንደሚደረግ መንግሥት መወሰኑ ተገልጿል፡፡ ይህ እንዴት ተግባራዊ ይሆናል የሚለው ጥያቄ ደግሞ መነሳቱ የግድ ነው፡፡ ከዚህ ቀደም በአገሪቱ ተከስቶ የነበረው አጠቃላይ የዋጋ ንረት እስከ 40 በመቶ ደርሶ እንደነበር የሚታወስ ሲሆን፣ የኅብረተሰቡን ኑሮ በምን ያህል ደረጃ አመሰቃቅሎት እንደነበርም አይዘነጋም፡፡ የዋጋ ንረቱ አሁን በነጠላ አኃዝ ላይ

በኢትዮጵያ የኣሜሪካን ኤምባሲ ባዘጋጀው የጆርናሊዝም ተማሪዎች ውድድር የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሶሰተኛነት ደረጃ ኣገኘ

Image
Cover caption:  Public Affairs Officer Robert Post (second from left) with winning students (left to right): Feven Abreham, Etsubdink Hailu and Endalekachew Abebe  Photo: US Embassy በኢትዮጵያ የኣሜሪካን ኤምባሲ ባዘጋጀው የጆርናሊዝም ተማሪዎች ውድድር የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሶሰተኛነት ደረጃ  ከማግኘቱ በላይ ከኤምባሲው የጆርናሊዝም እና የኮሙኒኬሽን መጽሐፍት ተለግሶለታል። ዝርዝር ዜናው የኣዲስ ስታንዳርድ ነው፦ The U.S. Embassy in Addis Ababa presented awards to three university students as part of the Embassy’s second Student Journalism Competition. The objective of the competition is to encourage students to gain practical experience in journalism that can be applied to their future careers.A panel of judges, including practicing journalists, reviewed the entries and judged them based on content, presentation, use of resources and research materials.  The competition was conducted among university and college students throughout the country. Students submitted stories that were published or broadcast in public or private media outlets.  The event w

A NEW MASTER PLAN:COMPLICATED-TURNED-DEADLY

Image
A recent plan to build a fantastic Addis Abeba is complicated and has turned deadly. It is not terribly late for a u-turn, but the first step may be the hardest: bringing justice to the dead     Kalkidan Yibeltal For a number of universities located in Ethiopia’s Oromia regional state, the largest state in the country, the month May was no ordinary month. It was a month marked by extraordinary exhibition of solidarity by the country’s ethnic Oromo students who protested the coming into effect of a master plan by the Addis Abeba City Administration (AACA). As is always the case with Ethiopia, the protests resulted in the regrettable (and unnecessary) loss of lives, destruction of properties and disruption of the academic schedule. If one is to stick by it, the government’s own account put the number of deaths at 11, of which seven were in Ambo, a town 120 km west of the capital Addis Abeba. Other deaths occurred in Meda Walabu University in Bale, 320 km southwest of the country;

ቡና እንደለሰላሰ መጠጥ

Image
NEW YORK ,  June 24, 2014  /PRNewswire/ -- Summer is here for many parts of the world and temperatures are on the rise with cold beverage consumption not far behind. Illy, the leader in coffee culture and innovator of coffee products, has explored its  MONOARABICA ™  Brazil  single origin whole bean coffee with cold brew preparation methods creating a distinct iced-coffee for the summer season for enjoyment in hotels, restaurants, and cafes in addition to home use. "Using illy single-origin beans from  Brazil  with different cold preparations, we have created a beautiful taste experience that transports coffee drinkers to an exotic tropical  savanna  south of the equator," said  Giorgio Milos , Master Barista for illy  North America . "Several cold brew preparations soften the natural acidity in the Brazilian beans that are more pronounced in hot preparation, resulting in a taste profile that enhances the caramel and milk chocolate notes of the bean."