በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ የጡት ካንስር ህክምና መሰጠት ሊጀመር መሆኑ ተሰማ

የጡት ካንሰር ህክምና በዩኒቨርሲቲዎች መሰጠት ሊጀመር ነው

የጡት ካንሰር ህክምናን በ5 ዩኒቨርሲቲዎች ለመጀመር የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን በጡት ካንሰር ዙሪያ የሚሰሩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ገለጹ።
ይህን ህክምና ለመጀመር የሚያስችል የመሳሪያና የባለሞያ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል።
ህክምናው የሚሰጠው በጅማ፣ ሃዋሳ፣ መቀሌ፣ ጎንደር እና ሃሮማያ ዩኒቨርሲቲዎች ነው።
ዓለም አቀፉ የጡት ካንሰር ቀን ጥቅምት 16 በተለያዩ ዝግጅቶች ሲከበርም አዲስ አበባን ጭምሮ በኦሮሚያ፣ አማራ፣ ደቡብ እና ትግራይ ክልሎች የእግር ጉዞ በማካሄድ ነው።
የዚህ በአል አላማ ህብረተሰቡ የጡት ካንሰርን አስቀድሞ የመከላከል፣ የምርመራና የህክምና አማራጮችን ግንዛቤ ማሳደግ ነው።
የጡት ካንሰር ህመምን ሙሉ ለሙሉ አስቀድሞ መከላከል ባይቻልም ህመሙ እንደተከሰት ተገቢው ህክምና ከተሰጠ የመዳን እድሉ  ሰፊ ነው።
የዕድሜ መግፋት፣ ከመጠን ያለፍ ክብደት፣ አልኮል መጠጣት፣ ጡት አለመጥባትና መሰል ምክንያቶች ለጡት ካንሰር እንደሚያጋልጥ የዘርፉ ባለሞያዎች ይናገራሉ።
ምንጭ፦ EBC

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር