የሁለቱ ምክር ቤቶት 4ኛው ዙር የመጨረሻው የስራ ዘመን የጋራ መክፈቻ ስነ ስርዓት ነገ ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ መስከረም 25፣ 2006 (ኤፍ.ቢ.ሲ.) የህዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የ4ኛው ዙር የመጨረሻው የስራ ዘመን  የጋራ መክፈቻ ስነ ስርዓት ነገ ይካሄዳል።
በመክፈቻ ስነሰርዓቱ ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሙላቱ ተሾመ ንግግር ያደርጋሉ።
በፕሬዚዳንቱ ንግግርም የ2007 ዓ.ም ዋና ዋና የመንግሰት የትኩረት አቅጣጫዎች ይዳሰሳሉ ተብሏል።
ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክው፥ በመክፈቻ ስነስርአቱ ላይ የሁለቱ ምክር ቤቶች አባላትና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይታደማሉ።
ስነ ስርአቱ በቴሌዥንና በሬድዮ በቀጥታ ይተላለፋል።

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር