የሁለቱ ምክር ቤቶት 4ኛው ዙር የመጨረሻው የስራ ዘመን የጋራ መክፈቻ ስነ ስርዓት ነገ ይካሄዳል
አዲስ አበባ፣ መስከረም 25፣ 2006 (ኤፍ.ቢ.ሲ.) የህዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የ4ኛው ዙር የመጨረሻው የስራ ዘመን የጋራ መክፈቻ ስነ ስርዓት ነገ ይካሄዳል።
በመክፈቻ ስነሰርዓቱ ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሙላቱ ተሾመ ንግግር ያደርጋሉ።
በፕሬዚዳንቱ ንግግርም የ2007 ዓ.ም ዋና ዋና የመንግሰት የትኩረት አቅጣጫዎች ይዳሰሳሉ ተብሏል።
ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክው፥ በመክፈቻ ስነስርአቱ ላይ የሁለቱ ምክር ቤቶች አባላትና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይታደማሉ።
ስነ ስርአቱ በቴሌዥንና በሬድዮ በቀጥታ ይተላለፋል።
Comments
Post a Comment