በውጪ የሚገኙ ተጫዋቾች ነሐሴ 18 ብሔራዊ ቡድኑን ይቀላቀላሉ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በሚቀጥለው ዓመት ለሚከናወነው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጳጉሜ 2 ቀን 2006 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ስታዲየም የአልጄሪያ አቻውን ያስተናግዳል፡፡
በአፍሪካ ለተለያዩ አገሮች ክለቦች በመጫወት ላይ የሚገኙ የቡድኑ ወሳኝ ተጫዋቾች ነሐሴ 18 አዲስ አበባ ገብተው ዝግጅት እንደሚጀምሩ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል፡፡ 
ፖርቱጋላዊው የዋሊያዎቹ አሠልጣኝ ማሪያኖ ባሬቶ ከአገር ውስጥ ክለቦች የመረጧቸውን ተጫዋቾች ይዘው በብራዚል ከተለያዩ ክለቦች ጋር የወዳጅነት ጨዋታ በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡ ለግብፅ፣ ለደቡብ አፍሪካና ለሱዳን ክለቦች የሚጫወቱት ሳላዲን ሰይድ፣ ኡመድ ኡክሪ፣ ጌታነህ ከበደና አዲስ ሕንፃ ፌዴሬሽኑ ከክለቦቻቸው ጋር ባደረገው ግንኙነት መሠረት በሚቀጥለው ሳምንት ብሔራዊ ቡድኑን እንደሚቀላቀሉ ይጠበቃል፡፡ 
በብራዚል ከተለያዩ ክለቦች ጋር የአቋም መለኪያው ጨዋታ እያደረገ የሚገኘው ብሐራዊ ቡድኑ እስከ ነሐሴ 17 ቀን ድረስ እንደሚቆይ ታውቋል፡፡ ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ ምንም እንኳ ያለው ነገር ባይኖርም፣ በስዊድን የሚጫወተው የሱፍ ሳላህ ዋሊያዎቹን እንዲቀላቀል አሠልጣኙ መጠየቃቸው ዘገባዎች አመልክተዋል፡፡ 

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር