የሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና ዛሬ መሰጠት ጀመረ መልካም እድል ለሲዳማ ተማሪዎች!

ምንጭ፦ www.fanabc.com
አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 19 ፣ 2006 (ኤፍ.ቢ.ሲ.) የ2ኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና ዛሬ በመላ ሀገሪቱ መሰጠት ጀመረ።
ፈተናውን 887 ሺህ 982 ተማሪዎች የወሰዱ ሲሆን ፥ ተማሪዎቹ  በዛሬው የፈተና መርሃ ግብራቸው አማርኛ ፣ እንግሊዘኛና ሂሳብ ትምህርቶችን መፈተናቸውን ነው የሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ የተናገረው።
በተዘጋጁት 1 ሺህ 494 የመፈተኛ ጣቢያዎች ውስጥም ያለምንም የዲሲፕሊን ጉድለት የመጀመሪያው ቀን የፈተና ሂደት መከናወኑን የኤጀንሲው ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዘሪሁን ዱሬሳ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል።
የሁለተኛው ቀን ፈተናም ሀሙስ ግንቦት 21 የሚቀጥል ሲሆን ፥ በሚቀጥሉት የፈተና ቀናት ውስጥም ህብረተሰቡና በፈተናው የተሳተፉ አካላት በዛሬው እለት ለፈተናው በሰላም መከናወን ያደረጉትን ጥረት አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የፊታችን ሰኞ ደግሞ ከ199 ሺህ በላይ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የሚፈተኑት የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ይቀጥላል።

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር