ሲኣን/መድረክ ግንቦት 16 በሃዋሳ ከተማ ሊያደርገው የነበረውን ስላማዊ ሰልፍ ለሰኔ 7 ቀን 2006 ኣስተላለፈ
የሲዳማ
ኣርነት ንቅናቄ/ ሲኣን
በሃዋሳ ከተማ በወቅታዊ ጉዳዮች እና የሎቄን
ሰማዕታት ቀን በሰላማዊ ሰልፍ ላማሰብ የጸጥታ ጥበቃ እንዲያደርግለት ያቀረበውን
የጽሁፍ ጥያቄ የከተማው ኣስተዳደር ባለመቀበሉ
የሰላማዊ ሰልፉን ቀን ወደ ሰኔ 7
ለማዛወር መገደዱ
ታውቋል።
ሪፖርተራችን
ጥቻ ወራና ሲኣንን ጠቅሶ እንደዘገበው፤ ድርጅቱ
ለከተማው ኣስተዳደር በጻፈው ደብዳቤ በከተማ
ኣስተዳደር የተሰጠውን ምላሽ እንደምቀበል
የገለጸ ሲሆን፤ የሰላማዊ ሰልፍ ማድረጊያውን
ቀን ወደ ሰኔ 7 ቀን
2006 ማዛወሩን
በመጠቆም በዚሁ ቀን የጸጥታ ጥበቃ እንዲደረግለት
በድጋሜ ጠይቋል።
ሲኣን/
መድረክ ለከተማ
ኣስተዳደሩ የጻፈውን ደብዳቤ ከታች ኣያይዘነዋል
ያንቡት፦
Comments
Post a Comment