በመላው ዓለም ላይ ያሉ ሲዳማውያን 12ኛ ዓመት የሎቄ ሰማዕታት ቀን በማሰብ ላይ ናቸው

የዛሬ 12 ኣመት ግንቦት 16  ህገመንግስታዊ መብቶቻቸውን በሰላማዊ መንገድ በጠየቁ ሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ በጠቅላይ ሚኒስትር ኣቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ይመራ የነበረው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ጸጥታ ኃይል በፈጸመው የጅምላ ጭፍጨፋ የተሰውትን የሎቄ ሰላማዊ ሰልፈኞች ቀን በተለይ በሃዋሳ እና በሎንዶን ከተማ በተለያዩ  ዝግጅቶች በመታሰብ ላይ መሆኑ ታውቋል።

የወራንቻ ኢንፎርሜሽን ኔትዎርክ ያሰባሰባቸው መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፤ ቀኑ በመላዋ ሲዳማ በተለይ በሃዋሳ፤ ቱላ፤ሞሮቾ፤ሌኩ፤ ይርጋኣለም፤ ኣለታ ጩኮ፤ ኣለታ ወንዶ፤ ዲላ እና ወንዶ ወሻ በተለያየ ደረጃ በመከበር ላይ ነው።

ከከተሞቹ የወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፤ የከተሞቹ ነዋሪዎች በቡድን እና በግለሰብ ደረጃ ቀኑን እያሰቡ ይገኛሉ። 

በሎንዶን ከተማ እና በሲዳማ ከተሞች የነበረውን ኣከባበር ዝርዝር መረጃ እንደደረሰን የምናቀርብ መሆናችንን ለመግለጽ እንወዳሃለን።


Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር