በመላው ዓለም ላይ ያሉ ሲዳማውያን 12ኛ ዓመት የሎቄ ሰማዕታት ቀን በማሰብ ላይ ናቸው
የዛሬ 12 ኣመት ግንቦት 16 ህገመንግስታዊ መብቶቻቸውን በሰላማዊ መንገድ በጠየቁ ሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ በጠቅላይ ሚኒስትር ኣቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ይመራ የነበረው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ጸጥታ ኃይል በፈጸመው የጅምላ ጭፍጨፋ የተሰውትን የሎቄ ሰላማዊ ሰልፈኞች ቀን በተለይ በሃዋሳ እና በሎንዶን ከተማ በተለያዩ ዝግጅቶች በመታሰብ ላይ መሆኑ ታውቋል።
የወራንቻ ኢንፎርሜሽን ኔትዎርክ ያሰባሰባቸው መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፤ ቀኑ በመላዋ ሲዳማ በተለይ በሃዋሳ፤ ቱላ፤ሞሮቾ፤ሌኩ፤ ይርጋኣለም፤ ኣለታ ጩኮ፤ ኣለታ ወንዶ፤ ዲላ እና ወንዶ ወሻ በተለያየ ደረጃ በመከበር ላይ ነው።
ከከተሞቹ የወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፤ የከተሞቹ ነዋሪዎች በቡድን እና በግለሰብ ደረጃ ቀኑን እያሰቡ ይገኛሉ።
በሎንዶን ከተማ እና በሲዳማ ከተሞች የነበረውን ኣከባበር ዝርዝር መረጃ እንደደረሰን የምናቀርብ መሆናችንን ለመግለጽ እንወዳሃለን።
Comments
Post a Comment