2ኛው ዙር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬና ነገ ይካሄዳል፤ ሃዋሳ ከነማ ከመብራት፧ ሲዳማ ቡና ከመከላከያ ይጫወታሉ

2ኛው ዙር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬና ነገ ይካሄዳል፤ ሃዋሳ ከነማ ከመብራት፧ ሲዳማ ቡና ከመከላከያ ይጫወታሉ መልካም እድል ለሲዳማ ክላቦች
አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 4 ፣ 2006 (ኤፍ.ቢ.ሲ.) ሁለተኛው ዙር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬና ነገ ይካሄዳል።
ዛሬ ወላይታ ዲቻ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 9 ሰዓት ላይ ሲገናኙ ፤ መብራት ሃይል ከሃዋሳ ከነማ በ11 ሰዓት ከ30 ላይ ይጫወታሉ።
ነገ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሙገር በአዲስ አበባ ስታዲየም 10 ሰዓት ላይ ይገናኛሉ።
አርባ ምንጭ ከነማ ከኢትዮጵያ መድህን ፣ ሲዳማ ቡና ከመከላከያ ፣ ዳሽን ቢራ ከሃረር ቢራ በተመሳሳይ 9 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ።
በሌላ በኩል ሊጠናቀቅ  አምስት ሳምንታት በቀረው በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ስቶክ ሲቲ ከኒውካስትል ፣ ስንደርላንድ ከኤቨርተን ፣ ዌስት ብሮም ከቶተንሃም በተመሳሳይ 11 ሰዓት 07 ላይ ይገናኛሉ።
ነገ የሊጉ መሪ ሊቨርፑል ሁለት ተስተካካይ ጨዋታ ካለውና በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ በሶስተኛነት ከተቀመጠው ማንቸስተር ሲቲ ጋር 9 ሰዓት ከ37 ላይ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው።
ቸልሲ በበኩሉ ከሜዳው ውጭ ስዋንሲን 12 ሰዓት ከ07 ላይ ይገጥማል።
በእንግሊዝ ኤፍ ኤ ካፕ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ዛሬ አርሰናል ከዊጋን አትሌቲክ ምሽት 1 ሰዓት ከ07 ላይ ጨዋታውን  ያደርጋል።
በፕሪሚየር ሊጉና በኤፍ ኤ ካፕ ጨዋታዎች የተጨመረው 7 ደቂቃ ፥ ከሃያ አራት አመታት በፊት ሊቨርፑል ከኖቲንግሃም ፎረስት ሲጫወቱ የደረሰውን የሂልስ ቦሮውን አደጋ ለማስታወስ መሆኑ ተገልጿል።
በ33ተኛው ሳምንት የስፔን ላሊጋ ዛሬ ግራናዳ ከባርሴሎና 3 ሰዓት ላይ ሲገናኙ ፤ ሪያል ማድሪድ ከአልሜሪያ ምሽት 5 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ።

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር