በመላ የደቡብ ክልል ጨዋታ የሚሳተፉ የስፖርት ልኡካን አርባምንጭ ከተማ እየገቡ ነው፤ መልካም እድል ለሁለት ተከፍለው ለምሳተፉ ለሲዴዎች

አርባምንጭ የካቲት 8/2006 በደቡብ ክልል በአርባምንጭ ከተማ ከነገ ጀምሮ በሚካሄደው መላ የደቡብ ጫዋታዎች ላይ የሚሳተፉ የስፖርት ልዑካን አርባምንጭ ከተማ በመግባት ላይ መሆናቸውን የዝግጅት ኮሚቴው ገለጸ።
የዝግጅት ኮሚቴው ሰብሳቢና የጋሞጎፋ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ጣሰው ጫቾ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ከአራት ሺህ የሚበልጡ ስፖርተኞችና የስፖርት ቤተሰቦች የሚሳተፉበትና ለሁለት ሳምንት በ17 የስፖርት ዓይነት ውድድር ይካሄዳል። 
የጋሞ ጎፋ ዞን ከአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲና ከተማ አስተዳደሩ ጋር በመቀናጀት ከክልሉ 15 ዞኖችና 4 ልዩ ወረዳ በጫዋታው የሚሳተፉ የስፖርት ልዑካንን ለማስተናገድ ሁሉን አቀፍ ዝግጅት አጠናቆ እንግዶችን በመቀበል ላይ መሆኑን ገልጸዋል።
እስከአሁን የአዋሳ ከተማ አስተዳደርን ጨምሮ የ12 ዞኖችና የሁለት ልዩ ወረዳ የስፖርት ልዑካን አርባምንጭ ከተማ ደርሰዋል።
በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ በአባያ ካምፓስ በሚገኘው ትልቁ ስታዲዮም ነገ በድምቀት በሚጀምረው የመክፈቻ ስነ ስርአት ላይ የክልሉን ርዕሰ መስተዳድር ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናትና የስፖርት ቤተሰቦች እንደሚገኙ ገልጸዋል።

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር