ቅዱስ ጊዮርጊስና ሲዳማ ቡና ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ

አዲስ አበባ የካቲት 12/2006 በኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ በ11ኛው ሳምንት ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ መሪነቱን አጠናከረ።
ቅዱስ ጊዮርጊስ  ትናንት ጨዋታውን  ከሐዋሳ ከነማን ጋር አድርጎ  1ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፉ ከሌሎች ቡድኖች ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ይበልጥ እያሰፋ ነው።
በኃይሉ አሰፋ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ብቸኛዋንና ለአሸናፊነት ያበቃቻቸውን ግብ አስቆጥሯል።
ቅዱስ ጊዮርጊስ  ዘጠኝ ጨዋታዎችን አድርጎ በ 27 ነጥብ አንዱንም ሳይሸነፍ የሊጉን መሪነት እንደያዘ ነው።
በሌላ በኩል  ሲዳማ ቡናና  ሙገር ሲሚንቶን በይርጋለም ላይ ባካሄዱት ጨዋታ ሲዳማ ቡና  2 ለ1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።አሁን ላይ  ሲዳማ ቡና 9 ነጥቦች ያሉት ሲሆን ይህን  ጨዋታ በማሸነፉ  ከወራጅ ቀጠና ለመውጣት ችሏል።
የቅዱስ ጊዮርጊሱ ኡመድ ኡክሪ በ9 ጨዋታዋች 9 ጎሎች በማስቆጠር የፕሪሚሪ ሊጉን የኮከብ ግብ አግቢነቱን እየመራ ይገኛል።

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር