የፊታችን ማክሰኞ ሀዋሳ ከነማ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ፤ ሲዳማ ቡና ከሙገር ሲሚቶ በተመሳሳይ 9 ሰዓት ላይ ይገናኛሉ፤ መልካም እድል ለሲዳማ ክለቦች!

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 8 ፣ 2006 (ኤፍ.ቢ.ሲ.) አስራ አንደኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ቀጥሎ ይካሄዳል።
ዛሬ መብራት ሃይል ከኢትዮጵያ መድን 8 ሰዓት ላይ ፤ ኢትዮጵያ ቡና ከዳሽን ቢራ 10 ሰዓት ላይ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይጫወታሉ።
ከነገ በስቲያ አርባ ምንጭ ላይ አርባምንጭ ከነማ ከሃረር ቢራ 10 ሰዓት ላይ ጫወታቸውን ያደርጋሉ።
የፊታችን ማክሰኞ ደግሞ ሀዋሳ ከነማ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ፤ ሲዳማ ቡና ከሙገር ሲሚቶ በተመሳሳይ 9 ሰዓት ላይ ይገናኛሉ።
በአፍሪካ ሻምፒየንስ ሊግና የኮንፌደሬሽን ዋንጫ ነገ ደደቢትናመከላከያ የመልስ ጫዋታቸውን ያደርጋሉ።
2 ለ0 የተሸነፈው መከላከያ የመልስ ጨዋታውን ነገ 10 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ያካሂዳል።
ደደቢት በበኩሉ ወደ ዛንዚባር ተጉዞ ነገ ከኬኤም ኬኤም ጋር የመልስ ጨዋታውን ያደርጋል።
በሌላ በኩል አምስተኛው ዙር የእንግሊዝ ኤፍ ኤ ካፕ ዛሬና ነገ ይካሄዳል።
ዛሬ 9 ሰዓት ከ45 ሰንደርላንድ ከሳውዝአምፕተን ሲጫወት ፤ ካርዲፍ ሲቲ ዊጋንን 12 ሰዓት ላይ ይገጥማል።
ትልቅ ግምት ባገኘው ጨዋታ ማንችስተር ሲቲ  በሜዳው ቼልሲን ምሽት 2 ሰዓት ከ15 ላይ ይፋለማል።
ነገ ደግሞ አርሰናል ሊቨርፑልን ምሽት 1 ሰዓት ላይ በሜዳው ያስተናግዳል።

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር