ጥቂት የሲዳማ የእግር ኳስ ክለቦች ተጨዋቾችን የያዘው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ብድን በቻን ውድድር ያለምንም ግብ ተሰናበተ

አዲስ አበባ፣ ጥር 14 ፣ 2006 (ኤፍ.ቢ.ሲ.) በደቡብ አፍሪካ እየተካሄደ ባለው 3ኛው የቻን አፍሪካ እግር ኳስ ውድድር ተሳታፊ የነበረው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ፥ የምድቡን የመጨረሻ ጨዋታ ትናንት ምሽት 2 ሰዓት ላይ ከጋና አቻው ጋር አድርጎ 1 ለ 0 ተሸንፏል።
ዋሊያዎቹ ምንም ጎል ሳያስቆጥሩ በአራት የጎል እዳ ከምድቡ ተሰናብተዋል።
ጋናዎች የምድብ ሶስት መሪ ያደረጋቸውን ሶስት ነጥብ ያስመዘገቡት በ76ኛው ደቂቃ ያገኙትን ፍፁም ቅጣት ምት ኩዋቢ አዱሴ ወደ ጎል በመቀየሩ ነው፡፡
በምድቡ ፥ ሊቢያ ኮንጎን በማሸነፍ  ጋናን ተከትላ ወደ ቀጣዩ ዙር የግማሽ ፍፃሜ ተቀላቅላለች፡፡

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር