በሲዳማ ዞን ከ1ሚሊዮን ለሚበልጡ የቤት እንስሳት ህክምናና ክትባት ሰጠሁ ኣለ
ሃዋሳ ጥር 6/2006 በሲዳማ ዞን ባለፉት ስድስት ወራት ከ1ሚሊዮን ለሚበልጡ የቤት እንስሳት የተለያዩ በሽታዎች መከላከያ ክትባትና ህክምና መሰጠቱን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ ።
በመምሪያው የግብርና ልማት እቅድ ኦፊሰር አቶ ደርቤ በትራ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በዞኑ የተለያዩ ወረዳዎች ያለውን የእንስሳት ሃብት በዘመናዊ መንገድ በማርባት አርሶ አደሮች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥረት እየተደረገ ነው ።
አርሶ አደሮቹ ከእንስሳት ሃብቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ በጤና አጠባበቅ ረገድ መንግስት በሰጠው ትኩረት ለ692 ሺህ057 እንስሳት የተለያዩ በሽታ መከላከያ ክትባት፣ ለ429ሺህ 586ቱ ደግሞ የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ መደረጉን አስታውቀዋል ።
ለቤት እንስሳቱ የበሽታ መከላከያ ክትባቱና ህክምናው የተሰጠው የእንስሳት ህክምና ባለሙያዎች ከቦታ ቦታ በመዘዋወርና በእንስሳት ጤና ከላዎች በመገኘት መሆኑን ተናግረዋል ።
የህክምና አገልግሎቱ የእንስሳት ሰውነት በማቁሰል ለሞት የሚዳርጉ የጎሮርሳ፣ የጉርብርብ፣የአባጎርባና አባሰንጋ፣ የሰንባ በሽታን ለመቆጣጠር የሚያስችል መሆኑን ገልፀዋል ፡፡
መምሪያው በዚህ አመት 156 ሺህ 700 የዳልጋ ከብቶች፣ ፍየሎችና በጎች በማድለብና በማሞከት ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘት መቻሉን አቶ በትራ ተናግረዋል፡፡
Comments
Post a Comment