Posts

Showing posts from January, 2013

ሲዳማ ብሔረሰብ

Image
የሲዳማ ብሔረሰብ በደቡብ ክልል ከሚገኙ ብሔረሰቦች መካከል አንዱ ነው። ሲዳማ የሚለው ቃል ለሕዝቡና ለመሬቱ የተሰጠ ስያሜ ሲሆን  «  ሲዳንቾ »  የሚለው ቃል ደግሞ ለሁለቱም ፆታዎች ሲዳማነታቸውን የሚገልጽ ነው፡፡ ብሔረሰቡ በዋናነት ከሚኖርበት አካባቢ ውጪ በኦሮሚያ ክልል በባሌ፣ በጉጂ፣ በምዕራብ አርሲ ዞኖች እና በክልሉ በወላይታና በጌዴኦ ዞኖች ውስጥ ይኖራል። የብሔረሰቡ ዋና የኢኮኖሚ መሠረት እርሻና ከብት እርባታ ሲሆን፤ አነስተኛ የዕደ ጥበብ እና የንግድ እንቅስቃሴዎች በተወሰኑ የማኅበረሰቡ ክፍሎች ይከናወናሉ። በብሔረሰቡ እንሰት፣ ቡና፣ በርበሬ፣ ጐመን፣ ሽንኩርት፣ በቆሎ፣ ስንዴ፣ ገብስ፣ ጤፍ፣ አጃ፣ ባቄላ፣ አተር፣ ቦሎቄ፣ አቦካዶ፣ አናናስ፣ ማንጐ፣ ሙዝ፣ ፓፓያ፣ አብሽ፣ ኮረሪማ፣ በሶብላ፣ ድንች፣ ስኳር ድንች፣ ቦይና፣ ሸንኮራ አገዳና ጫትን በዋናነት ያመርታል። የብሔረሰቡ ቋንቋ  « ሲዳምኛ »  ሲሆን ከምሥራቅ ኩሻዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ ይመደባል። ከካምባታ፣ ከጠምባሮ፣ ከኦሮሞ፣ ከሀላባ ከቀቤና እና ከጌዴኦ ቋንቋዎች ጋር ይቀራረባል። ብሔረሰቡ ከአፍ መፍቻ ቋንቋው በተጨማሪ አማርኛ፣ ኦሮምኛ እና ወላይትኛን ኩታ ገጠም በሆኑ አካባቢዎች ይጠቀማል። የሲዳማ ብሔረሰብ የራሱ የሆነ ባህላዊ አስተዳደርና የፍትህ ሥርዓቶች ያሉት ሲሆን፤ አጥፊዎች የሚዳኙበት  « ሴራ »  የተባለ ሕግ አላቸው። የባህላዊ አስተዳደሩ የበላይ አካል  « ወማ » ( ንጉሥ ) ነው። ሥልጣኑም በዙር የሚተላለፍ በመሆኑ እያንዳንዱ ጐሣ የራሱ ወማ አለው። በብሔረሰቡ በርካታ የጋብቻ ሥርዓቶች ያሉት ሲሆን  « ሁጫቶ »  በቤተሰብ ፈቃድ የተመሠረተ፣  « አዱልሻ »  ማስኮብለል፣  « ዲራ »  ጠለፋ፣  « ራጌ »  የውርስ ጋብቻ እና  « አዳዋና »  ሴቆ -  ቱጋ ሴት ልጅ ዕድ

The current regime and its policies in Sidama While noting some positive changes initiated by the current regime, ... The following are details of what has occurred in Sidama since the replacement of an overly arrogant central rule by a ...

Image
The current regime and its policies in  Sidama  While noting some positive changes initiated by the current regime,  ...  The following are details of what has occurred in Sidama  since the replacement of an overly arrogant central rule by a  ... Read more:  http://books.google.com.gt/books?id=sbddoOdnkyAC&pg=PA174&dq=sidama&hl=en&sa=X&ei=RjcJUZa8B4iu8ASjnYGwCw&ved=0CEcQ6AEwBg#v=onepage&q=sidama&f=false

ሃዋሳን ጨምሮ በክልሉ ከተሞች ከ130 የሚበልጡ የሸማቾች የህብረት ስራ ማህበራትና 32 ዩኒየኖች ምርቱን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ በማቅረብ ገበያን ማረጋጋት ስራውን በመቆጣጠር ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦን ማበረከታቸውን አስታውቀዋል፡፡

Image
በደቡብ ክልል ከ500 ሺህ ኩንታል የሚበልጥ ስኳርና ስንዴ ተሰራጨ አዋሳ ጥር 22/2005 በደቡብ ክልል በተጠናቀቀው ግማሽ የጀት ዓመት ከ500 ሺህ ኩንታል የሚበልጥ ስኳርና ስንዴ በማሰራጨት ገበያውን በማረጋጋት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የክልሉ ንግድ፣ ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ቢሮ ገለጸ፡፡ የቢሮ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ የኔወርቅ ቁምላቸው ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በክልሉ ያለውን ህብረተሰብ ከሚጎዱ የንግድ አሰራሮች በመከላከል ገበያን የማረጋጋቱ ስራ ውጤታማ ሆኗል፡፡ የክልሉ መንግስት መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎች ስርጭት የሚመራበትን አሰራር ቀይሶ በሁሉም አከባቢ የስራ መዋቅሮችን በመዘርጋት ባለፉት ስድስት ወር ከ508ሺህ 054 ኩንታል በላይ ስኳርና ስንዴ በማሰራጨት ገበያን የማረጋጋት ስራ ማከናወኑን አስታውቀዋል፡፡ ስርጭቱ ፍትሃዊና ተደራሽ በሆነ መንገድ የተከሄደው በየአከባቢው የሚገኙ የጅንአድ ቅርንጫፍ ማዕከላት፣ ከ14 ዞኖችና ከ22 የከተማ አስተዳደር በተመረጡ የጅምላ ንግድ ፈቃድ ባላቸው ነጋዴዎችና በተደራጁ የህብረት ስራ ማህበራት አማካኝነት ነው ብለዋል፡፡ በዘይት አቅርቦት በኩል የሚታየውን ችግር ለመቅረፍ በስምንት የጅንአድ ማዕከላትና በየከተሞች በተቋቋሙ ዩኒየኖች አማካኝነት ከ14 ሚሊዮን ሊትር በላይ የምግብ ዘይት ለተጠቃሚዎች መከፋፈሉን ተናግረዋል፡፡ በተለይ ሃዋሳን ጨምሮ በክልሉ ከተሞች ከ130 የሚበልጡ የሸማቾች የህብረት ስራ ማህበራትና 32 ዩኒየኖች ምርቱን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ በማቅረብ ገበያን ማረጋጋት ስራውን በመቆጣጠር ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦን ማበረከታቸውን አስታውቀዋል፡፡ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነትና ገበያን ለማረጋጋት የሚሰሩ ስራዎች ውጤታማ እንዲሆኑና ስርጭቱን ፍትሃዊ፣ ግልፅና ተደራሽ ለማድ

በዞኑ ከ14 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች ፈቃድ ወስደው ወደ ስራ ተሰማሩ

Image
አዋሳ ጥር 21/2005 በሲዳማ ዞን ባለፉት ስድስት ወራት ከ14 ሚሊዮን ብር በላይ የኢንቨስትመንት ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሃብቶች ፈቃድ ወስደው ወደ ስራ ተሰማሩ፡፡ የዞኑ ንግድና ኢንዱስትሪ መምሪያ የኢንቨስትመንት ማስፋፊያ ዋና የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ብርሃኑ ወልደሚካኤል ትናንት እንደገለጹት በግማሽ ዓመቱ አምስት ባለሃብቶች ፈቃድ በማውጣት ከ14 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ካፒታል ስራ ጀምረዋል፡፡ ባለሃብቶቹ ከተሰማሩባቸው የስራ መስኮች መካከል አገልግሎት መስጫ ተቋማት፣ ግብርናና ኢንዱስትሪዎች እንደሚገኙበት አመልክተዋል፡፡ ባለሃብቶቹ ለ88 ቋሚና 894 ዜጎች ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፍጠራቸውን ገልጸው አንዳንድ ከተሞች ላይ ባለፈው ዓመት የተጀመሩ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ከ5 ሺ ለሚበልጡ ዜጎች የስራ ዕድል መፍጠራቸውን አስረድተዋል፡፡ መምሪያው በገጠር የሚገኙ የኢንቨስትመንት አማራጮችን በማጥናትና በመለየት ለባለሃብቶች ከማስተዋወቅ በተጨማሪ በግብርና፣ በማህበራዊ አገልግሎትና በኢንዱስትሪ ዘርፍ ለተሰማሩ ባለሀብተቶች ከ600 ሄክታር በላይ የገጠር መሬት አዘጋጅቶ መስጠቱን የስራ ሂደቱ አስተባባሪ ተናግረዋል፡፡ እንዲሁም ለበርካታ ባለሃብቶች የፈቃድ እድሳትና ተጨማሪ የማስፋፊያ ፈቃድ መሰጠቱን ጠቁመው ከዚህ ቀደም ቦታ ወስደው ወደ ስራ ያልገቡ ባለሃብቶችን በመከታተልና ድጋፍ በመስጠት በፍጥነት ወደ ስራ የሚገቡበትን ሂደት ለማመቻቸት ባደረገው ጥረት 288 ፕሮጀክቶች የአገልግሎት ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡ አዲስ ፈቃድ ወስደው ወደ ስራ ከገቡት ባለሃብቶች መካከል አቶ ብርሃኑ አድማሱና አባተ አርጊሶ በሰጡት አስተያየት መንግስት ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋት እያደረገ ያለው ድጋፍና እገዛ በርካታ ባለሃብቶች በሀገር ውስጥ እንዲፈጠሩ አድርጓል፡፡ በተጨማሪም በድህነት ላይ ለሚደረ

Ethiopia: Who Is More Ethiopian?

COLUMN In every way, the political opposition parties of the 2005 elections were irresponsible hooligans who did not even know their own goals. Given their smear campaign, I have always wondered how they could have undertaken the job of governance had they succeeded in their quest for power. They were dividing the nation even before gaining votes. They were contradictorily promising tax cuts, whilst still planning to increase public spending. They lacked the minimum internal stability necessary for smooth administrative functioning. Amazingly, they also invited the international community to interfere in the internal affairs of the nation they were seeking to administer, with little concern for its sovereignty. I am always surprised to hear people lamenting about the 2005 elections, as if it was the turning point for Ethiopian democracy, whereas, rather, it was the point where our aspirations for democracy were crushed. By and large, Ethiopian minorities were deeply concer

ደኢህዴን በሲዳማ ዞንና በከተሞች የሚወዳደሩ ከ115ሺህ በላይ እጩዎችን ስያስመዘግብ ሲኣን ግን እስከኣሁን እጩ ኣላስመዘገበም ተባለ

Image
ሀዋሳ ጥር 20/2005 ሀዋሳ ከተማን ጨምሮ በሲዳማ ዞንና በሌሎች ከተሞች በመጪው ሚያዝያ ለሚካሄደዉ የአካባቢ ምርጫ ደኢህዴን ከ115 ሺህ በላይ እጩዎችን ማስመዝገቡን የዞኑ ምርጫ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በዞኑና በከተሞቹ ለሚካሄደዉ ምርጫ ከ1ሚሊዮን በላይ መራጮች መመዝገባቸውም ተገልጧል ። የጽህፈት ቤቱ አስተባባሪ አቶ ብርሃኑ ዱካሞ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ደኢህዴን ያስመዘገባቸው 115 ሺህ 368 ዕጩዎች ለዞን ፣ለወረዳ ፣ለከተማና ለቀበሌ ምክር ቤቶች ድርጅቱን ወክለው የሚወዳደሩ ናቸው። ደኢህዴን ለሲዳማ ዞን ፣ለሀዋሳ ፣ለይርጋለምና ለአለታ ወንዶ ከተሞች አስተዳደሮችና ለ21 ወረዳዎች ካስመዘገባቸው ዕጩዎች ውስጥ 105 ለዞን ምክር ቤት፣ 277 ለከተማ አስተዳደር ምክር ቤት፣ 1ሺ524 ለወረዳና ፣113 ሺህ 462 ለቀበሌ ምክር ቤት የሚወዳደሩ መሆኑን ተናግረዋል። ለምርጫው በዞኑና በከተማ አስተዳደሮች ፣በወረዳዎችና በቀበሌ ለመወዳደር ካስመዘገባቸው ዕጩዎች ውስጥ 53 ሺህ 289 ሴቶች ሲሆኑ ከነዚህ ዕጩዎች 38 ለዞን ምክር ቤት ፣110 ለከተማ ምክር ቤት፣ 484 ለወረዳ የሚወዳደሩ ሲሆን ቀሪዎቹ ለቀበሌ ምክር ምክር ቤት እንደሚወዳደሩ አስረድተዋል። በዞኑ ለመወዳደር ተመዝግበዉ የመለያ ምልክት ከወሰዱ አራት የፖለቲካ ፓርቲዎች ማለትም ደኢህዴን፣ ፣ሲአን፣ኢዴአፓና ኢራፓ ውስጥ እስካሁን ዕጩዎቹን ያስመዘገበው ደኢህዴን ብቻ መሆኑን አስተባበሪዉ አመልከተዉ የዕጩዎች ምዝገባ የሚጠናቀቀው በነገዉ እለት በመሆኑ ፓርቲዎቹ ዕጩዎቻቸውን እንዲያስመዘግቡ አሳስበዋል። በተጨማሪም በዞኑ በተቋቋሙ 1648 የምርጫ ጣቢያዎች እስካለፈው አርብ ድረስ 1 ሚሊዮን 33 ሺህ መራጮች መመዝገባቸውንና ከነዚህ ውስጥ 472 ሺህ 764 ሴቶች መሆናቸውን አቶ ብርሃ

በሲዳማ ዞንና ሃዋሳ ከተማ ከ955 ሺህ በላይ መራጮች ተመዘገቡ

Image
ሃዋሳ ጥር 20/2005 በደቡብ ክልል ሲዳማ ዞንና በሃዋሳ ከተማ በመጪው ሚያዝያ ለሚደረገው የአካባቢ ምርጫ ከ955 ሺህ በላይ መራጮች ተመዘገቡ፡፡ የሲዳማ ዞን ምርጫ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት አስተባባሪ አቶ ብርሃኑ ዱካሞ እንደገለጹት በዞኑ በሚገኙ 21 ወረዳዎችና በሃዋሳና ይርጋለም የከተማ አስተዳደሮች በሚገኙ 1 ሺህ 648 የምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች ምዝገባ ያለምንም ችግር በመከናወን ላይ ነው። እስከ ጥር 21 ድረስ በሚቆየው የመራጮችና የዕጩዎች ምዝገባ ከ1 ሚሊዮን 282 ሺህ በላይ መራጮች ይመዘገባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል። ከታህሳስ 22 ጀምሮ በመከናወን ላይ ባለው የመራጮችና የዕጩዎች ምዝገባ ለመራጭነት ከተመዘገቡት መካከል 446 ሺህ 699 ሴቶች መሆናቸውን ጠቁመዋል። በመጪው ሚያዝያ ወር በሚደረገው የአካባቢና የማሟያ ምርጫ ላይ በመራጭነት ለመሳተፍ የመራጮች ምዝገባ በመጪው ማክሰኞ ከመጠናቀቁ በፊት ህብረተሰቡ በመመዝገብ የመራጭነት ማረጋገጫ ካርዱን መያዝ እንዳለበት አስተባባሪው አሳስበዋል። በሃዋሳ ከተማ ሚሊኒየም ቀበሌና ዋጋኔ ዋጮ ቀበሌ ለመራጭነት በመመዝገብ ላይ ከሚገኙት መካከል ወይዘሮ በላይነሽ ደምሴና አቶ ታከለ ተሾመ በሰጡት አስተያየት ያገኙትን ዲሞክራሲያዊ መብት በመጠቀም የተሻለ ለውጥ በማምጣት ይሰራልናል ብለው ያመኑትን ዕጩ ለመምረጥ የመራጭነት ማረጋገጫ ካርድ ወስደዋል። http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=4931&K=1

በሃዋሳ ከተማ ከ7 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጭ የተገነባው የነዳጅ ማደያ አገልግሎት ጀመረ፡፡

Image
ሃዋሳ ጥር 20/2005 የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በማሳካት የኢንዱስትሪውን ልማት ለማፋጠን በሚደረገው ጥረት የልማታዊ ባላሃብቶች ተሳትፎ ከፍተኛ ድርሻ እንዳለዉ የደቡብ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈ ገባኤ አስታወቁ ፡፡ በሃዋሳ ከተማ ከሰባት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጭ የተገነባው ዳሎል ኦይል የነዳጅ ማደያ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡ ምክትል አፌ-ጉባኤ አቶ ማሞ ጎዴቦ ማደያውን መርቀው ስከፍቱ እንደተናገሩት ባለፉት ሁለት አስርት አመታት በግብርና፣ በከተማ ልማት፣ በኢንዱስትሪ፣ በመልካም አስተዳደር እንዲሁም በሌሎችመስኮች በክልሉ አመርቂ ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡ በየደረጃው ለተመዘገቡ ለውጦች መንግስታዊ አደረጃጀቶች፣ መላው ህብረተሰብ፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና የግል ባለሃብቶች በጋራ ያበረከቱት አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው ብለዋል ። በተለይ ይላሉ አቶ ማሞ ሁሉም ዜጋ በሀገሪቱ ውስጥ በሚከናወኑ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ውስጥ የድርሻቸውን እንዲወጡ መንግስት ያስቀመጣቸው ውጤታማ ፖሊሲዎችና ስትራቴጅዎች ለተመዘገበው ስኬት ቁልፍ ድርሻ አበርክተዋል፡፡ በዚህም በክልሉ ከ1986 ወዲህ ከ68 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ከአምስት ሺህ የሚበልጡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደው ወደ ስራ መሰማራታቸውንና ከአንድ ሚሊዮን ለሚበልጡ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፍጠራቸው ተናግረዋል፡፡ የሃዋሳ ከተማ ባለፉት ጥቅት አመታት ፈጣን ዕድገት እያስመዘገቡ ካሉ የሀገራችን ከተሞች አንዷ መሆኗን የጠቆሙት አቶ ማሞ የግል ባለሃብቶች ከከተማው ዕድገት ጋር የሚጣጣም የልማት አቅርቦት እንዲኖር ከመንግስት ጎን በመሆን እያበረከቱት ያለው አስተዋጽኦ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አስገንዝበዋል ። የዳሎል ኦይል አክሲዮን ማህበር

የሲዳማ ባህል እና ኣዲስ ኣመትን የተመለከተ በዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል የተዘጋጀ ዶክሜንትር

Image
Sidama's Culture and New Year

ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ከጌታ መንገድና ከኢህአዴግ መንገድ አንዱን መምረጥ ይኖርባቸዋል!

Image
የኢትዮጵያ ሕዝብ ጨረቃን ከሰማይ አውርዱልን እያለ አይደለም። የኢትዮጵያ ሕዝብ እያለ ያለው ግልጽነትን፣ ቀጥተኝነትን፣ ቅንነትንና ሀቀኝነትን አውርዱልን ነው። ዴሞክራሲን አውርዱልን ነው። ቁሳዊ ልማት ብቻውን አይበቃም፣ ሰብአዊና መንፈሳዊ ልማትንም አውርዱልን ነው። ዶ/ር ኃይሉ አርአያ የጌታ ኢየሱስ መንገድ ስል የክርስትና ሃይማኖት ዕምነት ቀኖናውን (ዶግማውን) ሳይሆን ክርስቶስ በዚህ ምድር ላይ ሲያስተምር ያሳየውን የቀናነት፣ የሃቀኝነት፣ የግልጽነት፣ የፍትሓዊነት፣ የእኩልነት፣ የአንድነት፣ የነፃነት፣ የዴሞክራሲያዊነት፣ የመተሳሰብ፣ የመፈቃቀር፣የመከባበር፣ የመተማመን... መንገድ ማለቴ ነው። ይህ መንገድ የክርስትና ሃይማኖት ብቻ ሳይሆን የእስልምና እንዲሁም የሌሎች የዓለም ታላላቅ ሃይማኖቶች መንገድ ነው። በዚህ መንገድ በሚመራ ህብረተሰብ ውስጥ በዕውቀት (በችሎታ) ማነስ ወይም በተራ ስህተት ወይም በስንፍና ካልሆነ በስተቀር ሆን ተብሎ፣ ታስቦና ታቅዶ በተንኮል በሚፈጸም ቂም በቀል፣ ግፍና በደል አገርና ሕዝብ አይጎዱም። የኢትዮጵያ ሕዝብ በዚህ መንገድ ቢመራ ከድህነትና ከኋላ ቀርነት የመላቀቅ፣ በዴሞክራሲያዊና ፍትሐዊ ሥርዓት የመመራትና በነፃነት፣ በሠላምና በአንድነት የክብር ኑሮ የመኖር ተስፋው እየራቀ ሳይሆን እየቀረበና እየለመለመ ይመጣል። የሚያሳዝነው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚመራው በዚህ መንገድ ሳይሆን በኢህአዴግ መንገድ ነው። የኢህአዴግ መንገድ ደግሞ በአብዛኛው ከላይ ከተገለጸው መንገድ የተለየ ነው። በእኔ እምነት የኢህአዴግ መንገድ ቀናነት፣ ግልጽነትና ሀቀኝነት የሚጎድለው መንገድ ነው። ከታሪካቸው እንደተረዳሁት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ከልብ አማኝ ክርስቲያን ና

የተቃዋሚዎች በምርጫው መሳተፍና አለመሳተፍ ትርፍም ኪሣራም እንደሌለው ኢህአዴግ ገለፀ

Image
ከሁለት ወራት በኋላ ይካሄዳል ተብሎ በሚጠበቀው የአዲስ አበባ አስተዳደርና የአካባቢ ምርጫ ላይ የተቃዋሚ ፓርቲዎች መሣተፍና አለመሳተፍ ለኢህአዴግ ትርፍም ኪሳራም እንደሌለውና የሚያጐድለው ነገርም እንደማይኖር ኢህአዴግ ገለፀ፡፡ የኢህአዴግ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሬድዋን ሰይድ ትናንት በፅ/ቤቱ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተናገሩት፤ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በአብዛኛው በአካባቢ ምርጫ ተሳትፈው አያውቁም፡፡ በአካባቢ ምርጫ የሚገኝ ሥልጣን በአብዛኛው ለታይታና ለወሬ የማይመች እና ሥራ ላይ ትኩረት ያደረገ በመሆኑ ተቃዋሚ ፓርቲዎቹ ፓርላማ መግባትን የመዋደቂያ ነጥብ አድርገው ሲንቀሣቀሱ ይታያሉ ብለዋል፡፡ የፓርቲዎቹ በምርጫው ላይ መሣተፍና አለመሳተፍ ትርፍም ኪሣራም የለውም ያሉት አቶ ሬድዋን፤ ለሥርዓቱ ግን መሣተፋቸው ጠቃሚ ይሆን እንደነበርና በምርጫው ውስጥ መሣተፋቸው ራሳቸውን ለማየትና ለመማር እንዲችሉ ያደርጋቸው እንደነበር ተናግረዋል፡፡ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች አንዳንዶቹ አንድ ግለሰብ በአራት ማህተም የሚያንቀሣቅሣቸውና በህይወት በሌሉ፣ የመጀመሪያውን ማህተም ባልመለሱ ሰዎች የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች እንደ ፓርቲ ተቆጥረው ምርጫ ውስጥ ገቡ አልገቡ ሊያሰኝ እንደማይችል ገልፀዋል። ብዙዎቹ ፓርቲዎች አባልም፣ ፅ/ቤትም እንደሌላቸው የተናገሩት ኃላፊው፤ እነዚህ ፓርቲዎች በምርጫው ቢሣተፉ ምንም እንደማይጠቅሙ ጠቁመው፤ ቀድሞውኑ የሚያንቀሣቅሱት ዓላማ ስለሌላቸው፤ ባይሣተፉ ደግሞ ምንም እንደማያጐሉ ምክንያቱም ቀድሞውኑ ያልነበሩ ስለሆነ ሲሉ ተናግረዋል፡፡ በምርጫው ውስጥ የብዙ ፓርቲዎች መሣተፍ የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት መገለጫ አይደለም ወይ በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄም፤ ምርጫው በ29 ፓርቲዎች መካከል የሚ

በሲዳማ የቀበሌ እና የኣካባቢ ምርጫ ላይ በምወዳደሩ የፖለቲካ ድርጅቶች ላይ ትኩረት ያደረገው ፕሮግራም

Image
ሲዳማ በዚህ ሳምንት

From The Orphanage To Punt, Pass & Kick Finals

Image
  7-Year-Old Hebron Boy's Soccer Skills Have Landed Him In The Finals Matiwos Rumley (Picasa, Hartford Courant ) January 2013 | Jeff Jacobs HEBRON — — A year ago, he was still sitting in an orphanage in Addis Ababa, one of five million Ethiopian orphans and vulnerable children. To be honest, sitting is probably the wrong word. For as the one-line description of Matiwos in his adoption portfolio read, "Lives to play, not to sit." Before Addis Ababa, Matiwos was in another orphanage, this one among his Sidama people in the Southern Nations section nearer to Kenya. The level of malnutrition, disease and lack of clean drinking water there is not some story for a television infomercial. It is a reality. And for the waiting children of Ethiopia, especially the older boys, another reality is they are rarely adopted. Yet here was Matiwos Rumley sitting the other day among his robust, loving family in a double-wing colonial in Hebron,

‹‹የምርጫ ምልክቴ የሆነውን አውራ ዶሮ ከምርጫ ቦርድ የወሰድኩት ሐዋሳን ጨምሮ የሲዳማ ሕዝብ ጥያቄው የክልል ጥያቄ ስለሆነ ሕዝቡ በዚህ ምርጫ ተሳትፎ በምርጫ ካርድ መብቱን ሊያስከብር ስለሚፈልግ የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ ወደ ምርጫ እንድንገባ ወስኗል›› የሲዳማ አርነት ንቅናቄ ፓርቲ ጸሃፊ አቶ ለገሰ ላቃሞ

Image
በመጪው ሚያዚያ ወር በሚካሄደው የአዲስ አበባ አስተዳደርና የአካባቢ ምርጫ የአፈጻጸም የጊዜ ሰሌዳ አስቀድሞ በምርጫው ፍትሃዊነት እና በሌሎች 18 አጀንዳዎች ላይ ሊወያዩ እንደሚገባ በማመን ፒትሽን ተፈራርመው ጥያቄያቸውን ለምርጫ ቦርድ ካስገቡ 33 ተቃዋሚ ፓርቲዎች አምስቱ የምርጫ ምልክታቸውን የወሰዱ ሲሆን 28ቱ ፓርቲዎች በቅርቡ ሕዝባዊ ስብሰባ እንደሚጠሩ አስታወቁ፡፡ የመድረክ ሥራ አስፈፃሚ አባልና የፓርቲዎች ሰብሳቢ አቶ አሥራት ጣሴ እንደገለፁት፤ ፓርቲዎቹ ጥር 26 ቀን 2005 ዓ.ም. ከሦስት በላይ የአዳራሽና የመስክ ሕዝባዊ ስብሰባ ለመጥራት ያቀዱ ሲሆን ለአዲስ አበባ መስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍና የስብሰባ ፈቃድ ክፍል ደብዳቤ ለማስገባት በዝግጅት ላይ ናቸው፡፡ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳውን በመቃወም ፒትሽን ከፈረሙት 33 ፓርቲዎች ውስጥ አምስቱ የምርጫ ምልክታቸውን እንደወሰዱ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል፡  ፡ የኢትዮጵያ ፍትህና ዲሞክራሲያዊ ሃይሎች ግምባር(ኢፍዲሃግ)፣ የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ሕብረት(ኢዲህ)፣ የባህር ወርቅ መስመስ ሕዝቦች ዲሞክራሲ ድርጅት(ባመህዴድ)፣ ዱቤና ደጀኔ ብሄረሰብ ዲሞክራሲያዊ (ዱብዴፓ) የሲዳማ አርነት ንቅናቄ ፓርቲ(ሲአንፓ) የምርጫ ምልክት መውሰዳቸውን ቦርዱ አስታውቋል፡፡ “በሲዳማ ዞን ሕዝብ ጥያቄ በምርጫ ለመሳተፍ ተገደናል” ያለው የሲዳማ አርነት ንቅናቄ ፓርቲ በበኩሉ የምርጫ ምልክት ወስዶ ለምርጫው ዝግጅት እያደረገ ቢሆንም በትግል ከ28ቱ ፓርቲዎች ጎን እንደሚሰለፍ ገልጿል፡፡ የ28ቱ ፓርቲዎች ሰብሳቢ አቶ አስራት ጣሴ ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት፤ “የምርጫ ቦርድ ፓርቲዎች ያቀረቡትን ጥያቄዎች ሳይመልስ ዐዋጁን ጥሶ ሕጋዊም፣ ሞራላዊም፣ ዲሞክራሲያዊ ባልሆነ መንገድ ለመድብለ ፓርቲ ሥርዓት መጠንከር ወሳኝነት ያላቸ

በሃዋሳ ከተማ እምብርት ላይ የቆመውን እና የሲዳማ ህዝብ ባህል የምተርከውን ሀውልት ስም በትክክል መጻፍ ያልቻለው ኣዲሱ የሃዋሳ ከተማ ኣስተዳደር ድህረገጽ

Image
ሙሉ ድረገጹን ለማየት እዚህ ላይ ይጫኑ: http://hawassacity.info/

Hawassa University(HwU) awarded honorary Doctoral Degree to Mr. Yohei Sasakawa

Image
Following Hawassa University’s Senate decision to bestow an Honorary Doctoral Degree to Mr.Yohei Sasakawa on July 14, 2012, Ethiopian ambassador to Japan His Excellency Mr. Markos Tekle awarded the Doctor of Agriculture Development Honoris Causa and Medal to Mr.Yohei Sasakawa, Chair of the Nippon Foundation,on an official ceremony held at the Ethiopian Embassy in Tokyo On December 12, 2012. Mr. Sasakawa was not able to travel to Ethiopia for health reasons. On the awarding ceremony held at Ethiopian Embassy in  Tokyo Japan, His Excellency Markos Tekle said Sasakawa Global has played a significant role in his country in minimizing the rate of famine, in enabling many people to be self- sufficient in food, in protecting natural resources and generally in the development of the country.  The ambassador added that the Sasakwa Program being financed by Nippon Foundation has brought many Sub- Sahara African countries out of poverty. According to Mr. Markos, it is realizing these su

ሲዳማን ጨምሮ በደቡብ ክልል ከሁለት ሚሊዮን 400 ሺህ የሚበልጥ ህዝብ ተመዝግቦ ካርድ መውሰዱ ተገለጸ

አዋሳ ጥር 08/2005 (ዋኢማ)  - በደቡብ ክልል በመጪው ሚያዝያ በሚካሄደው የአከባቢ ምርጫ እስካሁን ከሁለት ሚሊዮን 400 ሺህ የሚበልጥ ህዝብ ተመዝግቦ ካርድ መውሰዱን በብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ገለጸ።  ኃላፊው አቶ አብርሃም ገዴቦ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት እስከትናንት ከሁለት ሚሊዮን 400 ሺህ በላይ መራጮች ተመዝግበው ካርድ ወስደዋል፡፡  ካርድ ከወሰዱት መካከል አንድ ሚሊዮን 168ሺህ የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸውንም ገልጸዋል፡፡ መራጮቹ ምዝገባ ያደረጉት በክልሉ 14 ዞኖች፣ 4 ልዩ ወረዳዎችና በ22 የከተማ አስተዳደር በተቋቋመው 8ሺህ 130 ምርጫ ጣቢያዎች መሆኑን ገልፀው በክልሉ ሰባት ሚሊዮን መራጮች ይመዘገባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም አስታውቀዋል፡፡  በሁሉም ምርጫ ጣቢያዎቹ 40 ሺህ ስድስት መቶ ምርጫ አስፈፃሚዎች የምርጫውን ስራ ለማስፈፀም እየሰሩ መሆኑን ጠቁመው በተመሳሳይ ቁጥርም የህዝብ ታዛብዎች ተመርጠው እየሰሩ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡  የአከባቢ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነፃና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲካሄድ በየደረጃው የሚገኙ የመንግስት አስፈፃሚዎች፣ የሙያ ማህበራት፣ ህብረተሰቡና ሌሎች የባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን እንዲያበረክቱ ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል፡፡  የምርጫ አስፈፃሚዎች በበኩላቸው ህዝቡ ዛሬ ነገ ሳይል በመራጭነት ተመዝግቦ በህገ መንግስቱ የተረጋገጠለትን መብት መጠቀም እንዳለበት አሳስበዋል፡፡  http://www.waltainfo.com/index.php?option=com_content&view=article&id=7034:----400-----&catid=58:2011-08-29-12-55-21&Itemid=383

በ2005 ዓ.ም ለሚካሄደው የአካባቢና የከተማ ምርጫ 23 ሚሊዮን የሚጠጉ መራጮች ተመዝግበዋል

Image
አዲስ አበባ ጥር 14/2005 በመጪው ሚያዚያ ወር 2005 ዓ.ም ለሚካሄደው የአካባቢና የከተማ አስተዳደሮች ምርጫ የመራጮች ምዝገባ እንደቀጠለ ነው። በዘጠኙ ክልሎችና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች ከታህሳስ 22 እስከ ጥር 13 /2005 ዓ.ም ድረስ በተካሄደው የመራጮች ምዝገባ 23 ሚሊዮን የሚጠጉ መራጮች መመዝገባቸውን የምርጫ ቦርድ አስታወቋል፡፡ የቦርዱ የህዝብ ግንኙነት ማስተባበሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ይስማ ጅሩ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ከተመዘገቡት መራጮች መካከል 10 ሚሊዮን 794 ሺህ የሚሆኑት ሴቶች ናቸው፡፡ ቦርዱ በአጠቃላይ በሃገር አቀፍ ደረጃ ለመምረጥ ይመዘገባል ተብሎ ከሚጠበቀው ከ28 ሚሊዮን በላይ መራጭ መካከል 83 በመቶ የሚሆኑት የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውንም ጠቁመዋል፡፡ በተለያየ ምክንያት የመራጭነት ካርድ ያልወሰዱ መራጮችም በቀሪዎቹ 10 ቀናት የመራጭነት ካርዱን እንዲወስዱ ጥሪ አቅርበዋል። http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=4804&K=1

Ethiopia: Two Deadlines Gone, Only Five Collect Election Symbols

Legesse Lanikamo, secretary of the Sidama Liberation Movement, says his party decided to participate in the election "after a long discussion with the Sidama people," although he still vows allegiance to the cause of the 33 parties.   On the press conference held at the head office of the Blue party on Tuesday, Asrat Tase, the chairperson of the 33 parties and Gebru Gebremariam, executive member of Medrek, declared that they will be taking their case to the court if the election board does not accept their claim. Only five of the 33 parties that are in dispute with the National Electoral Board of Ethiopia, have collected their candidature symbols for the local election, which may not see the participation of the remaining 28 parties. The five that have joined the list are; the Ethiopian Justice & Democratic Front, Sidama Liberation Movement, Dube & Degeni Nations Democratic Party, Ethiopian Democratic Unity and Yebaher Work Mesmes People D