የሲዳማ እግር ኳስ ክለቦች በዚህ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ ውድድሮች ድል ቀንቶቸዋል
አዲስ አበባ ፣ ህዳር 29 ፣ 2006 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ዛሬ አዲስ አበባን ጨምሮ በክልል ከተሞች የተለያዩ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ተካሂደዋል።
አዲስ አበባ ላይ ቅዱስ ጊዮርጊስና ኢትዮጵያ ቡና ተገናኝተው ጊዮርጊስ 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
በተመሳሳይ መከላከያ ኢትዮጵያ መድንን 2 ለ 0 አሸንፏል።
አርባ ምንጭ ላይ የተገናኙት ወላይታ ዲቻና አርባ ምንጭ ከነማ 0 ለ 0 ተለያይተዋል።
አሰላ ላይ ሙገር ሲሚንቶን የገጠመው ሀዋሳ ከነማ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ሲያሸንፍ፥ ይርጋለም ላይ በተመሳሳይ ሲዳማ ቡና መብራት ሀይልን 1 ለ 0 አሸንፏል።
Comments
Post a Comment