ሰባተኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ሃዋሳ ከነማ ሲያሽንፍ ሲዳማ ቡና ሽንፈትን ኣስተናግዷል

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 6 ፣ 2006 (ኤፍ ቢ ሲ) ሰባተኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ትናንት እና ዛሬ በተለያዩ ከተሞች ተካሂደዋል።
በዛሬው ዕለት ከተካሄዱ ጨዋታዎች መካከል በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የመከላከያ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ጨዋታ በጊዮርጊስ አሸናፊነት ተጠናቋል።
በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም በተደረገው በዚህ ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፎ ወጥቷል።
ክልል ላይ በተደረጉ ጨዋታዎች ሃዋሳ ላይ ወላይታ ዲቻ ከ ሃረር ቢራ ያለምንም ግብ 0  ለ0 በሆነ ውጤት ተለያይተዋል።
እዛው ሃዋሳ ላይ በተደረገ ሌላ ጨዋታ ደግሞ ሃዋሳ ከነማ ዳሽን ቢራን 2ለ 0 ሲያሸንፍ ፤ አዲስ አበባ ላይ ንግድ ባንክ ሙገር ሲሚንቶን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
በአዲስ አበባ ስታዲየም ምሽት ላይ በተደረገ ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና ሲዳማ ቡናን 1 ለ 0 አሸንፏል።
ሊጉን ቅዱስ ጊዮርጊስ በ5 ጨዋታ 15 ነጥብ በመያዝ ሲመራ ፥ እኩል 7 ጨዋታ ያደረጉት መከላከያ እና ንግድ ባንክ በ14 ነጥብ ይከተላሉ።
የአምናው አሸናፊ ደደቢት በ4 ጨዋታዎች 10 ነጥብ ይዞ ይከተላል። 

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር