በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመክፈቻ ጫዎታ ሲዳማ ቡና ከኢትዮጵያ መድህን በመጫዎት ላይ ናቸው


የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2006 ዓ/ም የጨዋታ መርሃ ግብር በመጪው ቅዳሜ ጥቅምት 16/2006 ዓ/ም በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች በሚካሄዱ 5 ጨዋታዎች ይጀመራል፡፡
በፕሪሚየር ሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታ የተገናኙትና በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የደደቢትና የኢትዮጵያ ቡና ጨዋታ ህዳር 7 ዋሊያዎቹ ከናይጀሪያ ጋር ላለባቸው ወሳኝ ጨዋታ ተጫዋቾች ለብሔራዊ ቡድን በመጠራታቸው እንደተራዘመ ታውቋል፡፡
ከ10 በላይ ተጨዋቾችን ለዋሊያዎቹ ዝግጅት የተነጠቀው ቅዱስ ጊዮርጊስም ቅዳሜ ከሙገር ሲሚቶ ጋር የሚኖረው ጨዋታ ተራዝሟል፡፡
ፕሪሚየር ሊጉን በዚህ ዓመት የተቀላቀለው ዳሽን ቢራ በሜዳው ሐረር ቢራን የሚያስተናግድ ሲሆን እንደ ዳሽን ሁሉ በዚህ ዓመት ሊጉን የተቀላቀለው ወላይታ ዲቻ አዲስ አበባ ላይ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ይገጥማል፡፡
መብራት ሃይል በበኩሉ ወደ ሃዋሳ በማቅናት ሃዋሳ ከነማን እሁድ ሲገጥም መከላከያ ሲዳማ ቡናን እንዲሁም ኢትዮጵያ መድህን አርባ ምንጭን የሚያሰተናግዱበት ጨዋታ በመጀመሪያው ሳምንት ይጠበቃል፡፡
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ባለፈው ዓመት የተከሰተው የጨዋታዎች መቆራረጥ በዚህ ዓመትም ሊቀጥል እንደሚችል ቢሰጋም የውድድር መርሃ ግብሩ የተዘጋጀው እነዚን ውድድሮች ከግምት በማስገባት መሆኑን ፌደሬሽኑ ገልጿል፡፡
በውድድር ዓመቱ ዋሊያዎቹ የዓለም ዋንጫ የመጨረሻ ማጣሪያን ጨምሮ ለቻን አፍሪካ እንዲሁም ለሴካፋ የሚሳተፉ ይሆናል፡፡

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር