ካላ ደሴ ዳልኬ በወላይታ ዞን በሁምቦ ወረዳ ኣባያ ቢሳሬ ቀበሌ ነዋሪ በሆኑ የሲዳማ ተወላጆች ላይ በኣከባቢው ነዋሪዎች የሚፈጸሙ ወንጀሎች እንዲቆሙ ትዕዛዝ ሰጡ

ካላ ደሴ ዳልኬ የደቡብ ክልል ፕሬዚዳንት
ከኣንድ ወር በፊት በወላይታ ዞን በሁምቦ ወረዳ ኣባያ ቢሳሬ ቀበሌ ውስጥ ነዋሪ የሆኑ የሲዳማ ተወላጆች ላይ በኣከባቢው ነዋሪዎች የተለያዩ ወንጀሎች እንደተፈጸሙባቸው እና ቤት ንብረታቸውን በእነዚሁ ሰዎች መቃጠሉን ብሎም ኣከባቢውን በኣስቸኳይ እንዲለቁ በምል የማስፈራሪያ ዛቻ እንደደረሳቸው በቪድዮ የተደገፈ መረጃ በማቅረብ የሲዳማ ዞን መንግስት እና የቦርቻ ወረዳ ኣስተዳደር መፍትሄ እንዲፈልግላቸው ጥሪ ማቅረባችን ይታወሳል።

በጉዳዩ ላይ ሪፖርተራችን ጥቻ ወራና ታማኝ ምንጭ ጠቅሶ ከሃዋሳ እንደዘገበው፤ እነዚሁ በቤትንብረታቸው ላይ ጉዳት የደረሰባቸው የሲዳማ ተወላጆች 18 ተወካዮችን መርጠው ወደ ሃዋሳ በመላክ ለደቡብ ክልል ፕሬዚዳንት ለካላ ደሴ ዳልኬ ኣቤቶታ ኣቅርበዋል።

የተጎጂዎቹን ተወካዮች በቢሮቸው ተቀብለው ያነጋገሩት የክልሉ ፕሬዚዳንት ካላ ደሴ፤ በኣስቸኳይ ጉዳይ ኣጣሪ ቡድን በመሰዬም እና ቡድኑን ወደ ቀበሌው በመላክ የወንጀሉ መፈጸም ኣለመፈጸም እንድጣራ ማድረጋቸው ታውቋል።

ኣጣሪ ቡድኑ ባቀረበው ሪፖርት በሲዳማ ተወላጆች ላይ ወንጀል መፈጽሙን በማረጋገጡ፤ ካላ ደሴ ዳልኬ በኣከባቢው ነዋሪዎች የወደሙ ቤቶች እንድገነቡ እና በኣከባቢው ተወላጆች በሲዳማዎች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች በኣስቸኳን እንዲቆሙ ትዕዛዝ መስጠታቸው ተገልጸዋል።

ፕሬዚዳንቱ በሰጡት ትዕዛዝ መሰረት በኣከባቢው ያለውን ችግር የመፍታት ስራ በመሰራት ላይ ሲሆን፤ ህዝቡም በመረጋጋት ላይ ነው ተብሏል።


ኣዲሱ የክልሉ ፕሬዚዳንት ካላ ደሴ ዳልኬ ተጎጂዎቹ ያቀረቡትን ኣቤቶታ በመስማት እና በኣስቸኳይ መፍትሄ በማፈላለግ ሀላፊነታቸውን በመወጣታቸው እና ለተጎጂ የሲዳማ ተወላጆች ኣጋሪነታቸውን በማሳየታቸው መደሰታቸውን ተጎጂዎቹ መግለጻቸውን ሪፖርተራችን ጥቻ ወራና ዘግቧል።

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር