የሲዳማ ዞን መንግስት የካቢኔ ሽግሽግ _ የቀድሞ የዞኑ የድርጅት ፖለቲካ ሀላፊ የዞኑ ዋና ኣስተዳደር

የሲዳማ ዞን መንግስት የካቢኔ ሽግሽግ ኣድርጓል። የቀድሞ  የዞኑ ዋና  ኣስተዳደር ኣቶ ሚሊዮን ማቲዎስ ወደ ደቡብ ክልል ትምህርት ቢሮ ሃላፊነት የተዛወሩ ሲሆን፤ በእሳቸው ቦታ የቀድሞ የዞኑ ድርጅት ፖለቲካ ሃላፊ ካላ ኣክልሉ ኣደላ የዞኑ ዋና ኣስተዳደር ሆነዋል። በተጨማሪም በዞኑ ፋይናንስ መምሪያ በዋና ሃላፊ በመሆን ሲያገለግሉ  የቆዩት ኣቶ  በቀለ ታፎ ወደ ስቪል ስርቪስ መምሪያ  ሃላፊነት ተዛውረዋል።

በተመሳሳይ ዜና በሃዋሳ ከተማ ኣስተዳደርም የካቢኔ ሽግሽግ የተደረገ ሲሆን፤ የከተማው ፍይናንስ መምሪያ  ኣዲስ ሃላፊ ተሹሞለታል።

በዞኑ ስለተላሄደው የካቢኔ ሽግሽግ እና በሽግሽጉ ዙሪያ የተሰበሰበ የህዝብ ኣስተያየት እንደደረሰን ለክቡራን ኣንባብያን እንደምናቀርብ መግለጽ እንወዳለን ወራንቻ ኢንፎርሜሽን ኔትዎርክ

  

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር