የሪፖርተር ጋዜጣ በውሽት ዜና ብዙዎችን ማስደሰቱን ኣመነ፦ የደቡብ ክልል ሦስት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሮች ከኃላፊነታቸው አልተነሱም

የደቡብ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥትን በምክትል ርዕሰ መስተዳደርነት ከሚመሩት አራት ኃላፊዎች መካከል ሦስቱ ከኃላፊነታቸው ተነሱ በሚል ባለፈው ረቡዕ ነሐሴ 29 ቀን 2005 ዓ.ም. የተጻፈው ዘገባ ስህተት መሆኑን እየገለጽን፣ ሦስቱም በኃላፊነታቸው ላይ መሆናቸውን እናስታውቃለን፡፡
አሁንም በኃላፊነታቸው ላይ ያሉት ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ታገሠ ጫፎ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የክልሉ መንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ አለማየሁ አሰፋና ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳኒ ረዲ ናቸው፡፡ 
የደቡብ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ለሪፖርተር በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ ዘገባው ፍፁም የተሳሳተና የክልሉ መንግሥት የማያውቀው በመሆኑ የክልሉን መንግሥትና ሕዝብ አሳዝኗል፡፡ ‹‹ይህ የተሳሳተ ዘገባ የወጣው የክልሉ መንግሥት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ሆኖ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራትን በአንድ መንፈስ እያካሄዱበት በሚገኝበት ወቅት መሆኑ፣ ዘገባውን እጅግ የሚያሳዝንና የሚያስገርም ከማድረግ ባሻገር ይህ ተግባር በክልሉ እየተካሄደ ያለውን መጠነ ሰፊ ልማትና የሕዝብ ተጠቃሚነት ይጐዳል፤›› ሲል የክልሉ መንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት አስታውቋል፡፡ 
በወቅቱ ዘገባውን ያቀረበው የክልሉ የሪፖርተር ልዩ ዘጋቢ መረጃ በመሰብሰብ፣ በማጠናቀርና ዘገባውን በማቅረብ ሒደት ላይ ስህተት መሥራቱን የዝግጅት ክፍሉ በመረዳቱ፣ ዘጋቢውን በማገድና በጉዳዩ ላይ ተገቢውን ማጣራት አድርጎ ተገቢውን ዕርምጃ ለመውሰድ በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ ሆኖም ነሐሴ 29 ቀን 2005 ዓ.ም. በወጣው ዕትም የተዘገበው ስህተት መሆኑን እየገለጽን የክልሉን መንግሥት፣ ሦስቱን ምክትል ርዕሰ መስተዳድሮችንና አንባቢያንን ከልብ ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡ 

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር