በደቡብ ክልል ከ12ሺህ 400 በላይ የባዪ ጋዝ ተቋማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

ሃዋሳ ሐምሌ 27/2005 በደቡብ ክልል በተጠናቀቀዉ በጀት አመት የ12ሺህ 415 የባዮ ጋዝ ተቋማት ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን የክልሉ ውሃ ሀብት ቢሮ አስታወቀ ። የቢሮ የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች የስራ ሂደት ባለሙያ አቶ ጁሲ ጥላሁን ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት የባዮ ጋዝ ተቋማቱ ግንባታ እየተካሄደ ያለዉ አማራጭ የሀይል አቅርቦትን ለህብረተሰቡ ለማዳረስ መንግስት በያዘው ፕሮግራም መሰረት ነዉ ። በተጨማሪ በክልሉ የተለያዩ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች በሚገኙ የገጠር አካባቢዎች 193ሺህ ማገዶ ቆጣቢ ምድጃዎችን በማሰራጨት ከ190ሺህ ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል ። የባዮ ጋዝ ተቋማቱ የግብርና ተረፈ ምርቶችን በማብላለት ከሚወጣዉ ጋዝ በርካታ ቤተሰቦችን የመብራትና የምግብ ማሰያ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ አገልጠዋል ። በክልሉ አማራጭ የሃይል አቅርቦት ለህብረተሰቡ ለማዳረስ በተደረገው ጥረት ባለፉት አመታት በተመሳሳይ በርካታ የገጠር ነዋሪዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን አስታዉቀዋል ። ይህም ለማገዶና ለሀይል ፍላጎት እየተባለ የሚወድመውን የደን ሀብት ከመታደግ በሻገር የህብረተሰቡን የስራ ጊዜ ፣ ጉልበትና ወጪ ለመቆጠብ ከፍተኛ አስተዋጾኦ አድርጓል ብለዋል ። በደቡብ ክልል በእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመኑ መጨረሻ ታዳሽና አማራጭ የሀይል አቅርቦት በ2002 ከነበረበት 15 በመቶ ሽፋን ወደ 25 በመቶ ለማሳደግ ሰፋፊ ፕሮግራሞች ተነድፈው እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል ። በበጀት አመቱ ለኢነርጂና ለማእድን ልማት ጨምሮ የሚስፈልገው አጠቃላይ የማስፈጸሚያ በጀት ከ19ሚሊዮን ብር በላይ መሆኑን በእቅዱ ላይ ተመልክቷል፡፡

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር