የአቶ ሽፈራው ሽጉጤ ወደ ፌዴራል መንግሥት ሚኒስትርነት መምጣት በደቡብ ክልል ላይ ጊዜያዊ ክፍተት የፈጠረ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ለክልሉ ፕሬዚዳንትነት የስድስት ግለሰቦች ስሞች እየተነሱ ነው፡፡

የአቶ ሽፈራው ሽጉጤ ወደ ፌዴራል መንግሥት ሚኒስትርነት መምጣት በደቡብ ክልል ላይ ጊዜያዊ ክፍተት የፈጠረ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ለክልሉ ፕሬዚዳንትነት የስድስት ግለሰቦች ስሞች እየተነሱ ነው፡፡
ከእነዚህ መካከል ከሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትርነታቸው በመነሳት በኦሮሚያ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወ/ሮ ደሚቱ ሃንቢሳ የተተኩት አቶ ደሴ ዳልኬ አንደኛው ናቸው፡፡ ሌሎቹ በጃፓን የኢትዮጵያ አምባሳደር የሆኑት አምባሳደር ማርቆስ ተክሌና በአሁኑ ወቅት የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት በመሆን የሚያገለግሉት አራት ግለሰቦች ናቸው፡፡ 
እነሱም አቶ ታገሰ ጫፎ፣ አቶ ዓለማየሁ አሰፋ፣ አቶ ሳኒ ረዲና አቶ ደበበ አሰፋ ናቸው፡፡ ግምት ከተሰጣቸው መካከል የበለጠ ከፕሬዚዳንትነት ሥልጣኑ ጋር በተደጋጋሚ ስማቸው እየተጠራ የሚገኘው አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ ሲሆኑ፣ በሁለተኛ ደረጃ አቶ ደሴ ዳልኬ ሊሆኑ ይችላል የሚል ግምት አለ፡፡
ባለፈው ሐሙስ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የከፍተኛ መንግሥት ባለሥልጣናትን ሹመት በፓርላማ አፀድቀዋል፡፡ የአሥሩ አዲስ ተሿሚዎች ሹመት የፀደቀው በአንድ ድምፅ ተአቅቦና በአብላጫ ድምፅ ነው፡፡
ተሿሚዎቹ በጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ተገኔ ጌታነህ አማካይነት ቃለ መሃላ ፈጽመዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ባለፈው ረቡዕ አቶ በረከት ስምዖንና አቶ ኩማ ደመቅሳ በሚኒስትር ማዕረግ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፖሊስ ጉዳዮች አማካሪ ሆነው መመደባቸው ተገልጿል፡፡ 
በቅርቡ በፓርላማ የትምህርት ሚኒስቴርን የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ሲያቀርቡ በዘርፉ ለሚታዩ ችግሮች ከሚኒስትር ጀምሮ እስከታች ያሉ አመራሮችን የወቀሱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የትምህርት ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፣ በአቶ ኃይለ ማርያም አዲስ ሹመትና ሽግሽግ ከትምህርት ሚኒስትርነታቸው ተነስተዋል፡፡
‹‹ከሚኒስትር ጀምሮ ከፍተኛ አመራሮች መንጠባጠብ ይታይባቸዋል፡፡ መካከለኛ አመራሩ ደግሞ የለውጡን ሥራ መመርያና ትዕዛዝ ሰጥቶ ሪፖርት የመቀበል አሠራር አድርጐ የመቁጠር መሠረታዊ የአመለካከት ችግር አለበት፡፡ እንዲሁም ሥራውን በሚፈለገው ብቃት፣ መጠንና ጥረት ለመፈጸም የሚያስችል የአቅምና የክህሎት ችግር በመካከለኛ አመራሩ የሚስተዋል ነው፡፡ ሠራተኛው ደግሞ አዳዲስ አሠራሮችን ለመቀበል መጠራጠር፣ የጠባቂነት ስሜትና ከተለመደው አሠራር ያለመውጣት በዋናነት የሚስተዋል ችግር ነው፤›› በማለት በትምህርት ዘርፉ ለታዩ ችግሮች በምክንያትነት በሪፖርታቸው አቅርበዋል፡፡ 
ይህንን ባቀረቡ አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ የሥልጣን ሽግሽግና አዲስ ሹመቶችን ፓርላማው እንዲያፀድቅላቸው የጠየቁት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም፣ በመጀመሪያ ደረጃ አቶ ደመቀ መኮንን በተደራቢነት ከሚሠሩት የትምህርት ሚኒስቴር መነሳታቸውን ገልጸዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም የሰጡት ምክንያት አቶ ደመቀ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ላይ እንዲያተኩሩ በመፈለጉ ከትምህርት ሚኒስትርነታቸው እንዲነሱ መወሰኑን ነው፡፡
የአቶ ደመቀን የትምህርት ሚኒስትርነት ቦታ እንዲይዙ የተደረጉት የደቡብ ክልል ፕሬዚዳንት በመሆን እስካሁን ሲሠሩ የነበሩት አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ናቸው፡፡
አቶ ሽፈራው በተቋማዊ አስተዳደር የማስተርስ ዲግሪ ያላቸው መሆኑን፣ የተሾሙበት ተቋምን በብቁ ሁኔታ መምራት እንደሚችሉ በቅርበት የሚያውቃቸው ይናገራሉ፡፡ 
የአቶ ሽፈራው ሽጉጤ ወደ ፌዴራል መንግሥት ሚኒስትርነት መምጣት በደቡብ ክልል ላይ ጊዜያዊ ክፍተት የፈጠረ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ለክልሉ ፕሬዚዳንትነት የስድስት ግለሰቦች ስሞች እየተነሱ ነው፡፡
ከእነዚህ መካከል ከሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትርነታቸው በመነሳት በኦሮሚያ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወ/ሮ ደሚቱ ሃንቢሳ የተተኩት አቶ ደሴ ዳልኬ አንደኛው ናቸው፡፡ ሌሎቹ በጃፓን የኢትዮጵያ አምባሳደር የሆኑት አምባሳደር ማርቆስ ተክሌና በአሁኑ ወቅት የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት በመሆን የሚያገለግሉት አራት ግለሰቦች ናቸው፡፡ 
እነሱም አቶ ታገሰ ጫፎ፣ አቶ ዓለማየሁ አሰፋ፣ አቶ ሳኒ ረዲና አቶ ደበበ አሰፋ ናቸው፡፡ ግምት ከተሰጣቸው መካከል የበለጠ ከፕሬዚዳንትነት ሥልጣኑ ጋር በተደጋጋሚ ስማቸው እየተጠራ የሚገኘው አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ ሲሆኑ፣ በሁለተኛ ደረጃ አቶ ደሴ ዳልኬ ሊሆኑ ይችላል የሚል ግምት አለ፡፡
በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሹመት የሚኒስትርነት ሥልጣን ያገኙት የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ዳይሬክተር ጄነራል የነበሩት አቶ ወርቅነህ ገበየሁ ናቸው፡፡ የአዲስ አበባ ከንቲባ እንደሚሆኑ የሚጠበቁትን የትራንስፖርት ሚኒስትሩን አቶ ድሪባ ኩማን ተክተዋል፡፡
አቶ ወርቅነህ ለረጅም ዓመታት በብሔራዊ መረጃና ደኅንነት ተቋም በመቀጠልም የፌዴራል ፖሊስን ከሰባት ዓመት በላይ በኮሚሽነርነትና በዳይሬክተር ጄኔራልነት  አገልግለዋል፡፡ አቶ ወርቅነህ ረዥም ዓመታትን በደኅንነት ሥራ ላይ ያሳለፉ ከመሆናቸው አንፃር ውስብስብ የአስተዳደር ሥራንና የውጭ ዲፕሎማሲን በሚጠይቀው፣ እንዲሁም የሲቪል አቪዬሽንን በሚያካትተው የትራንስፖርት ሚኒስትር መሾማቸው በርካቶችን እያነጋገረ ይገኛል፡፡ 
የአማራ ክልል ምክትል መስተዳድር የነበሩት አቶ አህመድ አብተው የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ሆነው ሲሾሙ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር የነበሩትና የኢሕአዴግ አባል ሳይሆኑ በመንግሥት ሥልጣን ላይ ለረዥም ዓመታት የቆዩት ብቸኛው ግለሰብ አቶ መኮንን ማንያዘዋል እንደአዲስ ለተቋቋመው ብሔራዊ ፕላኒንግ ኮሚሽን በኮሚሽነርነት ተሹመዋል፡፡ 
አቶ በረከት ስምዖን በሚኒስትርነት ሲመሩት ለነበረው የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት አቶ ሬድዋን ሁሴን ሲሾሙ፣ አቶ ሬድዋን የኢሕአዴግ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ከመሆናቸው አንፃር ሹመቱ የተጣጣመ እንደሆነ ይነገራል፡፡ 
በሌላ በኩል በቅርቡ ለተቋቋመው የአካባቢና ደን ሚኒስቴር አቶ በለጠ ታፈረ ተሹመዋል፡፡ በፓርላማ ረዳት የመንግሥት ተጠሪ ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩት ወ/ሮ ሮማን ገብረ ሥላሴ የመንግሥት ተጠሪ ሚኒስትር በመሆን የወ/ሮ አስቴር ማሞን ተክተዋል፡፡ 
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የሰሞኑ ሹመትና ሽግሽግን ኢሕአዴግ ከጀመረው የመተካካት ሒደት ጋር የሚያገናኙት ሲኖሩ፣ በሌላ በኩል አቅም ባላቸው ከመተካት ጋር የሚያያይዙት አሉ፡፡ በፓርቲው ውስጥ ለረጅም ዓመታት የሠሩ ሰዎች ወደ አማካሪነት መመደባቸውን በመተካካቱ ሒደት ከመንግሥት ሥራ እየወጡ መሆኑን ማሳያ ነው የሚሉም ተሰምተዋል፡፡

Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር