ሲዳማን ጨምሮ ከደቡብ ክልል ዘንድሮ ከ83 ሺህ 100 ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ቀረበ

ሃዋሳ ሐምሌ 16/2005 በደቡብ ክልል በተጠናቀቀው የበጀት አመት 83 ሺህ 140 ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን የክልሉ ግብይትና ህብረት ስራ ቢሮ ገለጸ፡፡ በቢሮው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች የስራ ሂደት ባለቤት አቶ መላኩ እንዳለ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ቡናው የቀረበው በክልሉ ቡና አምራች ከሆኑ የተለያዩ ዞኖች በሚገኙ 380 የህብረት ስራ ማህበራትና ከ330 በሚበልጡ የግል ባለሃብቶች እንዲሁም የቡና ተክል ልማት ድርጅት አማካኝነት ነው፡፡ በዘመኑ ለማዕከላዊ ገበያ ገበያ ከቀረበው ከዚሁ ቡና ውሰጥ 42 ሺህ 189 ቶን የታጠበና ቀሪው 40 ሺህ 951 ቶን ደግሞ ያልታጠበ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ በስራው ላይም 394 የቡና ማዘጋጃ ኢንዱስትሪዎች ተሳትፈዋል፡፡ ክንውኑ የእቅዱን 68 በመቶ መሸፉኑንና ከአምናው ተመሳሳይ ጊዜ ጋር ሲነጻጸር ብልጫ እንዳለው ጠቁመዋል፡፡ ከዕቅዱ ሊያንስ የቻለው ህገ ወጥ የቡና ግብይትና ዝውውር መበራካት እንዲሁም የአለም ገበያ ዋጋ መቀነስና መዋዥቅ ጋር ተያይዞ ቡና አምራቹ ገበሬና አቅራቢው ወደፊት ዋጋው ይጨምራል በሚል በክምችት መያዙ አቶ መላኩ በምክንያትነት ከጠቀሱት ውስጥ ይገኙበታል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ከክልል እስከ ቀበሌ በየደረጃው የተቋቋመው የቡና ጥራትና ንግድ ቁጥጥር አሰተባባሪ ግብረ ሀይል በማጠናከር ህገ ወጥ ንግድ እንዲቆም ለማድረግ በዘመኑ በተካሄደው እንቅሰቃሴ ጀንፈል፣ መርቡሽ፣ እሸት ቡና ጨምሮ ከ21 ሺህ 700 ኩንታል በላይ ቡና ከህገ ወጦች ተይዞ ከ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ በህጋዊ መንገድ በመሸጥ ለመንግስት ገቢ መሆኑን የስራ ሂደቱ ባለቤቱ ጨምረው ገልጸዋል፡፡

Comments

Post a Comment

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር